የሳዑዲ አረቢያ አርጂንቲናን ማሸነፍ በስፖርቱ ዓለም ግርምታን አሳደረ

አርጀንቲና በፊፋ እግርኳስ ደረጃ ዓለም ሶስተኛ ደረጃ ላይ ያለች ሲሆን፤ ሳዑዲ አረቢያ 51ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።

Argentina v Saudi Arabia.jpg

Lionel Messi of Argentina shows their dejection as Saudi Arabia players celebrate the 2-1 win during the FIFA World Cup Qatar 2022 Group C match between Argentina and Saudi Arabia at Lusail Stadium on November 22, 2022 in Lusail City, Qatar. Credit: Clive Brunskill/Getty Images

በሊዮኔል ሜሲ አምበልነት የተመራውና በ1978 እና በ1986 ለሁለት ጊዜያት የዓለም ዋንጫ ባለቤት የሆነው የአርጀንቲና ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን በዛሬው ዕለት በሳዑዲ አረቢያ ኳታር ላይ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ተረቷል።

ግቦቹን ያስቆጠሩት በአርጀንቲና በኩል በ10ኛው ደቂቃ ሊዮኔል ሜሲ ሲሆን፤ በሳዑዲ አረቢያ በኩል በ48ኛው ደቂቃ ሳሌህ አል - ሺህሪና በ53ኛው ደቂቃ ሳሌም አል-ዳውሳሪ ናቸው።

ለዋንጫ ተፋላሚ ሊሆን ይችላል ተብሎ የተገመተው የደቡብ አሜሪካ ቡድን በመካከለኛው ምሥራቅ ቡድን መረታት በመላው ዓለም የስፖርት ተቺዎች ዘንድ ግርምታን አስከትሏል።

አርጀንቲና ቀደም ሲል ሳዑዲ አረቢያን ሁለት ጊዜ ያሸነፈችና ሁለቴ አቻ የወጣች ሲሆን፤ ይህ የመጀመሪያ ሽንፈቷ ነው።


1 min read

Published

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now