ባዩሽ ዓለማየሁ በአገር ፍቅር ቴአትር ቤት በተዋናይትነት ለረጅም አመታት አገልግላለች።
በርካታ አጫጭር ተከታታይ ድራማዎችን፣ ትረካዎችን፣ የመድረክ ትያትሮች ላይም በተዋናይነት እንዲሁም በአዘጋጅነት ስትሰራ ቆይታለች፡፡
ደራሲ፣ አዘጋጅና ተዋናይት ባዩሽ ዓለማየሁ እጅግ ጥቂት ከሚባሉ ሴት ፀሃፌ ተውኔቶችና አዘጋጆች ተርታ የምትመደብ ሲሆን በአገር ፍቅር ቴአትር ቤት በተዋናይትነት ለረጅም ዓመታት አገልግላለች።
ብዙዎች በመድረክ አተዋወኗ ብቃቷ የምትደነቀው ባዩሽ
- የቬኑሱ ነጋዴ
- የስለት ልጅ
- ሰማያዊ አይን ትዳር ሲታጠን
- ሰዓት ዕላፊ
- ነቃሽ ...በትወና የተሳተፈችባቸው ተውኔቶች ውስጥ ጥቂቶቹ ናቸው።
ረመጥ እና ፎርፌ እንዲሁም ገፅ ሁለት የተሰኙ ተውኔቶችንም ደርሳለች።
ባዩሽ ገጣሚና ተራኪም ጭምር የነበረች ሲሆን ፓፒዮ የተሰኘውን ረጅም ልብ ወለድ ድርሰት እና ሌሎችንም ስራዎች በሬዲዮ ፋና ተርካለች።
ባዩሽ ዓለማየሁ የታዋቂው ተርጓሚና ደራሲ መስፍን ዓለማየሁ ልጅ ናት።
በሕመም አልጋ እስከምትይዝበት ዕለት ድረስ በአገር ፍቅር ቴአትር ቤት በድጋሚ ሊታይ በነበረው ሰዓት ዕላፊ በተሰኘው የቴዎድሮስ ተ/አረጋይ ተውኔት ላይ በልምምድ ላይ ነበረች ተብሏል።
አርቲስቷ ባጋጠማት ህመም ምክንያት በህክምና ስትረዳ ቆይታ ነው ትናንት ታህሳስ 23/2013 ዓም ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ በህክምና ስትረዳ በቆየችበት በየካቲት 12 ሆስፒታል ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች።