"በአንድነት ስንቆም አገራችን ይበልጡን ለስኬትና ዕድገት ትበቃለች" - ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን

*** እንግሊዝኛ ቋንቋ ለማኅበራዊና ምጣኔ ሃብታዊ ተካታችነት ብርቱ መሳሪያ ነው - እንግሊዝኛ ቋንቋ ፓስፖርት ነው - ጠ/ሚ ስኮት ሞሪሰን

Budget 2020/21 PM

PM Scott Morrison Source: SBS Amharic

ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን ዛሬ ማለዳ ላይ የSBS አማርኛ ፕሮግራምን አካትቶ በጠሩት ጋዜጣዊ መግለጫ ትናንት ይፋ የሆነውን የፌዴራል በጀት 2020/21 አስመልክተው ማብራሪያ ሰጥተዋል።  

አቶ ሞሪሰን በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ሳቢያ የመላው ዓለም ምጣኔ ሃብት ለድቅቀት እንደበቃ ጠቁመው የአውስትራሊያ ጠቅላላ ምርት ዕድገትም በሰባት ፐርሰንት ማሽቆልቆሉን ገልጠዋል። ሆኖም የአውስትራሊያ ምጣኔ ሃብት ከሌሎች በርካታ ያደጉ አገራት ጋር ሲነጻጸር በተሻለ ሁኔት ላይ እንደሚገኝ አመላክተዋል።

ከምጣኔ ሃብታዊ ድቅቀቱ አገግሞ ለመውጣት በጀቱ ያተኮረባቸውን ሶስት ዋነኛ ጉዳዮች ሲያነሱ፤

  • አውስትራሊያን ገጥመዋት ያሉት ምጣኔ ሃብታዊ ተግዳሮች
  • የምጣኔ ሃብት ማገገሚያ ፕላን
  • የመካከለኛና የረጅም ጊዜ ዕቅዶች መሆናቸውን አስታውቀዋል።
በወረርሽኙ ሳቢያ ባለፉት ወራት ተከልተው ወይም ወደ ዜሮ ሰዓታት ወርደው የነበሩ 760 ሺህ ሥራዎች ዳግም መመለሳቸው ያስደሰታቸው መሆኑንም ተናግረዋል።

አውስትራሊያ በመድብለ ባሕል ፖሊሲ ትግበራዋ ስኬታማ መሆኑን በማንሳትም መጤዎች ጠያቂዎች ሳይሆኑ ታትሪ ሠራተኞችና ሥራ ፈጣሪዎች መሆኗቸውን አስገንዝበዋል። አያይዘውም፤ "ሁላችንም በአንድነት ስንቆም አገራችን ይበልጡን ለስኬትና ዕድገት ትበቃለች" በማለት በመጤዎችና በቀድሞ ነዋሪዎች መካከል ልዩነት ሳይኖር ሁሉም በእኩል ዜግነት መንፈስ በአውስትራሊያዊነታቸው እንዲቆሙና ለጋራ ዕድገት የዜግነት አስተዋፅዖዎቻቸውን እንዲያበረክቱ አሳስበዋል።

በማከልም፤ የእንግሊዝኛ ቋንቋን ጠቀሜታ አስመልክተው ሲናገሩ "እንግሊዝኛ ቋንቋ ለማኅበራዊና ምጣኔ ሃብታዊ ተካታችነት ብርቱ መሳሪያ ነው - እንግሊዝኛ ቋንቋ ፓስፖርት ነው" ብለዋል።

የዓለም አቀፍ ድንበር ከፈታን በተመለከተም በቅድሚያ ከኒውዝላንድ ጋር ቀጥሎም ከኮሪያ፣ ጃፓንና ሲንጋፖር ጋር ሁኔታዎች በፈቀዱ መልክ ዓለም አቀፍ ድንበሮችን ለመክፈት ዕቅድ መኖሩን ጠቁመዋል። እንዲሁም በሚቀጥለው ዓመት ዓለም አቀፍ ተማሪዎች ወደ አውስትራሊያ የሚመጡበት መንገዶች እየተመቻቹ እንደሆነና ሆኖም በጥድፊያ የሚከናወን አለመሆኑን ገልጠዋል።     

 

 


Share

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service