የቻይና ለአውስትራሊያ የእንወያይ ምላሽ ነፈጋ አሳሳቢ ሆኗል

አውስትራሊያ ወደ ቻይና የምትልካቸውን የሥጋና የገብስ የውጭ አቅርቦት አስመልክታ በሁለቱ አገራት መካከል ሰፍኖ ያለውን የንግድ ውጥረት ለማርገብ የእንወያይ መልዕክት ብትልክም እስካሁን ምላሽ አልተቸራትም። ይህም በሌሎች ኢንዱስትሪዎች ላይ ተፅዕኖን ሊያስከትል ይችላል የሚል ስጋትን አሳድሯል።

China ignores requests for talks after suspending imports from Australian meat processors

Chinese - Australian flags Source: SBS

ቻይና በአራት የአውስትራሊያ የእርድ ሥጋ አቅራቢ ድርጅቶች ላይ የጣለችውን ዕገዳ አስመልክቶ በቻይና ሚዲያ በኩል ለአውስትራሊያ "የማንቂያ ደወል" ስለመሆኑ እየተስተጋባ ነው።

የአውስትራሊያ ንግድ ሚኒስትር ሳይመን በርሚንግሃም ለእንወያይ ጥያቄያቸው በቻይና በኩል እስከ ዛሬ ረቡዕ ምላሽ እንዳልተሰጣቸው ተናግረዋል።

"ለምን ምላሽ እንዳልሰጡን ይህ ነው ለማለት አልችልም። በእኔ በኩል በሬ ክፍት ነው፤ ተግናኝቶ ለመነጋገር ዝግጁና ፈቃደኛ ነኝ"

"የቻይና የንግድ ሚኒስትርን ለውይይት ጠይቄያለሁ፤ እስካሁን ምንም ምላሽ የለም። ይሁንና የግንኙነት መስመራችንን ክፍት አድርገን እንቆያለን" ብለዋል።
China ignores requests for talks after suspending imports from Australian meat processors
Trade Minister Simon Birmingham. Source: AAP
በሁለቱ አገራት መካከል ያለው ግንኙነት ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መነሻን አስመልክቶ ምርምራ ይካሄድ ብለው ሉላዊ ዘመቻ ከጀመሩ ወዲህ ለውጥረት ተዳርጓል።

ቻይና በአራቱ የሥጋ አቅራቢዎች ላይ የጣለችው ዕገዳ የአውስትራሊያን 35 ፐርሰንት የከብት ሥጋ የውጭ አቅርቦት የያዘ ነው።

አሥራ ስምንት ፐርሰንት የአውስትራሊያ የከብት ሥጋ የውጭ አቅርቦት ምርት የሚላከው ወደ ቻይና ሲሆን፤ ለአውስትራሊያ የሚያስገኘው ገቢም በዓመት $3 ቢሊየን ነው።

ቀደም ሲልም ቻይና ወደ አገሯ በሚላከው የአውስትራሊያ የገብስ የውጭ አቅርቦት ላይ የ80 ፐርሰንት ታሪፍ ጥላለች።    

ይሁንና የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ዛዎ ሊያን ማክሰኛ ምሽት የቻይና እርምጃ ከአውስትራሊያ የኮሮናቫይረስ ምርመራ ድጋፍ ጋር ተያያዥነት እንደሌለው ገልጠዋል።

ለዕገዳው እርምጃ አስባብ የሆነው የጉምሩክ መኮንንኖች የጥራት ቁጥጥር ሲያካሂዱ የተወሰኑ የአውስትራሊያ የከብት ሥጋ አቅራቢዎች "ተደጋጋሚ ጥሰቶችን" ፈጽመው በመገኘታቸው እንደሁ ጠቁመዋል። 

አያይዘውም፤

"በቻይና በኩል በአውስትራሊያ ወገን ችግሩን አስመልክቶ ሙሉዕ ምርመራ ተካሂዶ ጉዳዩ ዕልባት እንዲያገኝ ተጠይቋል" ብለዋል።
China ignores requests for talks after suspending imports from Australian meat processors
Chinese Foreign Ministry spokesman Zhao Lijian attends a press conference in Beijing. Source: Kydpl Kyodo
የአውስትራሊያ የሥጋ ኢንዱስትሪ ምክር ቤት የዕገዳውን ምክንያት ከምርት ዝርዝር መግለጫ ጉዳይ ጋር አያይዞታል።

ሆኖም የናሽናልስ ፓርቲ ምክር ቤት አባል ጆርጅ ክሪስቲንሰን ግና የቻይናን ድርጊት ከጠበኝነትና የኃይል ጫና አሳዳሪነት ጋር አያይዘው ሲናገሩ፤

"ቻይና በአሁኑ ወቅት እያደረገች ያለችው በጣሙን አሳስቦኛል። ዋነኛ ኢንዱስትሪዎቻችንን እየጎዱብን ነው። ይህ ጠበኝነትና ኃይል የተመላው የጫና ድርጊት ነው፤ ይህ እንዲህ ባለ መልኩ መቀጠል የለበትም" ሲሉ ለ SBS News ተናግረዋል።
China ignores requests for talks after suspending imports from Australian meat processors
Nationals MP George Christensen Source: SBS


የብሔራዊ ገበሬዎች ፌዴሬሽን ፕሬዚደንት ፊዮና ሲምሰን በበኩላቸው የውጭ አቅርቦቱ መስተጓጎል አሳስቢ መሆኑን ገልጠዋል።

አክለውም፤

"በአውስትራሊያና ቻይና መካከል ያለው ግንኙነት በጣሙን ጠቃሚ መሆኑንና አልፎ አልፎም አንዳንድ ነገሮች እንደሚከሰቱ እንገነዘባለን"

"ሲከሰቱም ሁለቱ ወገኖች መከባበር በተመላበት ሁነት በተቻለ ፍጥነት ለሁለቱም አርኪ በሆነ መንገድ እክሉን መክላት አለባቸው" ሲሉ ምክረ ሃሳባቸውን አክለው ተናግረዋል።
China ignores requests for talks after suspending imports from Australian meat processors
NFF President Fiona Simson Source: AAP
የሌበር የግብርና ቃል አቀባይ ጆ ፊትዝጊበን በፊናቸው ለንግድ መስተጓጎሉ ክስተት የፌዴራል መንግሥቱ የራሱ ድርሻ እንዳለው ሲያመላክቱ፤

"መንግሥት ዋነኛ ከሆነች የንግድ ሽርካችን ጋር ያለውን ግንኙነት ሲያዛንፍ እንዲህ ያሉ የምጣኔ ሃብት መዘዞችን እንደሚያስከትል መጠበቅ ይቻላል" ብለዋል።
China ignores requests for talks after suspending imports from Australian meat processors
Labor's spokesperson for agriculture Joel Fitzgibbon Source: SBS
በዚህ ወር መጀመሪያ በካንብራ የቤጂንግ አምባሳደር ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን በምርመራ ጥሪያቸው ከቀጠሉ ቻይናውያን የአውስትራሊያን የክብት ሥጋና ገብስን መሸመቱ ላይ ቆም ብለው ሊያስቡ ይችሉ ይሆናል ማለታቸው ይታወሳል። 

የንግድ ሚኒስትር ሳይመን በርሚንግሃም የአውስትራሊያ ምርመራ ይደረግ ግፊት ከከብት ሥጋና ገብስ የውጭ ምርት አቅርቦት ጋር እንደማይያያዝ ተስፋቸውን ገልጠዋል።

የቻይና ግሎባል ታይምስ በበኩሉ፤ የቻይና እርምጃ አውስትራሊያን በምጣኔ ሃብት ለመቅጣት ተደርጎ ሊወሰድ እንደማይገባ ጠቁሞ "ቻይና ለአውስትራሊያ መጠነ ሰፊ የውጭ ምርት አቅርቦቶች ብቸኛ ምርጫ ስትሆን፤ አውስትራሊያ ግና ለቻይና ብቸኛ አማራጭ አይደለችም" ብሏል።

 

 


Share

Published

Updated

By Tom Stayner
Presented by Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service