በአውስትራሊያ የቻይና አምባሳደር አውስትራሊያ 'ጥንቃቄ' የተመላበት ድርጊት እንድትከውን አሳሰቡ

ታዝማኒያን ከታይዋን ጋር አነፃፀሩ

Ambassador Xiao Qian.jpg

China’s ambassador to Australia Xiao Qian compared Taiwan to Tasmania in a speech to the National Press Club in Canberra. Credit: AAP / MICK TSIKAS/AAPIMAGE

በአውስትራሊያ የቻይና አምባሳደር ሺያኦ ችየን የአውስትራሊያ በታይዋን ጉዳይ ጣልቃ መግባት ከወዲሁ ውጥረት ግብቶት ያለውን የአውስትራሊያ - ቻይና ግንኙነት ይበልጡን ሊጎዳ እንደሚችል አሳሰቡ።

አምባሳደሩ ይህን ያሉት በዛሬው ዕለት በአውስትራሊያ ብሔራዊ ፕሬስ ክለብ ተገኝተው ንግግር ባደረጉበት ወቅት ነው።

ቻይና የዩናይትድ ስቴትስ አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲን የታይዋን ጉብኝት ተከትሎ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን በታይዋን ባሕረ ሰላጤ ያካሔደች ሲሆን፤ የወታደራዊ ሚሳይል ውንጨፋዎቿም የአካባቢውን ሰላምና መረጋጋት ለውጥረት ዳርጓል።

በቤጂንግ ዕይታ ግና ወታደራዊ እንቅስቃሴዎቿ ለአፈ ጉባኤዋ ያልተወደደ ጉብኝት አግባብ ያለው ስለመሆኑ ተመልክቷል።

ይሁንና የቤጂንግ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች "ከመጠን ያለፈ አፀፋ" እና በአካባቢው ሰላምና መረጋጋት ላይ "ውጥረት" ፈጣሪ ነው በሚል በአውስትራሊያ በኩል በተቃራኒው ተገልጧል።

አምባሳደር ሺያኦ ግና የአውስትራሊያ የአፈ ጉባኤ ፔሎሲን የታይፔ ጉብኝት ደግፎ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ማበር ተገቢ አይደለም ሲሉ ተችተዋል።

አክለውም፤ የአውስትራሊያ መንግሥት የታይዋንን ጉዳይ 'በጥንቃቄ" እንዲይዝ አሳስበዋል። የቻይና አንድ አውራጃ በሆነቸው ደሴት ጉዳይ "ምንም ዓይነት የመቻቻል ሥፍራ አይኖርም" ሲሉም በከረረ ድምፀት ተናግረዋል።

ደሲቱትን ከእናት አገርዋ ጋር "ለማዋሃድ" ቻይና "ማናቸውንም አስፈላጊ እርምጃ ሁሉ" እንደምትወስድ በግልፅ አስቀምጠዋል።

China announced six exclusion zones around Taiwan.jpg
China announced six exclusion zones around Taiwan for military drills after the visit of US House Speaker Nancy Pelosi. Credit: SBS News

አያይዘውም፤ የአውስትራሊያ መንግሥት በ'አንድ ቻይና ፖሊሲ' ረግቶ እንዲቀጥል ዳግም አሳስበዋል።

ንፅፅራዊ ምሳሌነቱ መልካምነት እንደሚጎድለው አመላክተውም "ታዝማኒያ የአውስትራሊያ አካል ትሆናለች፣ ነበረችም፤ ናትም" ብለዋል።


1 min read

Published

Updated

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS



Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now