በፍርድ ቤቶች አሰራር ላይ የሚፈለገው ለውጥ አልመጣም ተባለ

*** የኢትዮጵያ ፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት የሕግ የበላይነትና በፍትህ አካላት ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየመከረ ነው

Court Reforms

Source: PD

ባለፉት ሁለት ዓመታት ተኩል በፍርድ ቤቶች ላይ የአሰራር ማሻሻያ ቢደረግም፤ የሚፈለገው ለውጥ አለመምጣቱን የሕግ ባለሙያዎች ገለጹ፡፡

የኢትዮጵያ ፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት የሕግ የበላይነትና በፍትህ አካላት ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየመከረ ነው፡፡

በምክክሩ ላይ አገሪቷ ለውጥ ውስጥ ከገባች ጊዜ ጀምሮ በሕግ የበላይነትና በፍትህ ዘርፍ ላይ የተከናወኑ ሥራዎች ሕዝብ በሚፈልገው ደረጃ  ላይ አለመሆናቸው ተገልጿል፡፡

በተለይ ፍርድ ቤቶች ላይ የነበረው የተንዛዛና በሙስና የተሳሰረ አሰራር ተባብሶ መቀጠሉን ባለሙያዎቹ ተናግረዋል፡፡

በኢትዮጵያ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ የፍትህ አካላትን አለመጠናከራቸውንም አስተያየት ሰጪዎቹ ገልጸዋል፡፡

የሚመለከታቸው አካላትየፍትህ ዘርፍ ሰብዓዊና ለዴሞክራሲያዊ መብቶች መከበር ባለው ድርሻ ቅድሚያ  እንዲሰጡትም ተጠቁሟል፡፡

ኢንስቲትዩቱ ከባለሙያዎቹ የሚያገኛቸውን ግብዓቶች ዘርፉን ለማሻሻል በሚደረጉ ጥናቶች እንደሚጠቀምባቸው ተመልክቷል፡፡

[ ኢዜአ ]


1 min read

Published

By Stringer


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now