ቪክቶርያ ምንም አይነት የኮሮናቫይረስን ሳታሳይ 23 ቀናትን አስቆጥራለች፡፡
ይህንኑ ተከትለው የቪክቶርያ ፕሪምየር ዳንኤል አንድሪውስ ተጨማሪ ገደቦች መላላታቸውን ይፋ አድርገዋል
- 25 % የሚሆኑ እና በግል ድርጅቶች የሚሰሩ ከኖቬምበር 30 በኋላ ወደ ስራ ገበታቸው ይመላሳሉ
- በመኖሪያ ቤት ከሰኞ ጀምሮ እስከ15 ሰዎችን ማስተናገድ ይቻላል
- ከመኖሪያ ቤት ወጭ እስከ 50 ሰዎች በአንድ ላይ መሰባሰብ ይችላሉ
- የፊት መሸፈኛ በሁሉም ቦታ ግዴታነቱ ቀርቶ ቦታ እየተመረጠ የሚደረግ ይሆናል
ይህ በእንዲህ እንዳለ የሜልበርን ከንቲባ ሳሊ ካፕ ከተማዋ የሜልበርን ነዋሪዎች እና በከተማ አካባቢ የሚሰሩ ሰራተኞችን በደስታ ለመቀበል መዘጋጀቷን አስታውቀዋል ፡፡
Share

