በፓርላማ መቀመጫ ያለው ፓርቲ የሚያገኘው የምረጡኝ ቅስቀሳ የአየር ሰአት ከ60 በመቶ ወደ 5 በመቶ እንዲቀንስ ሃሳብ ቀረበ

*** ተወዳዳሪ ፓርቲው ከፓርላማ መቀመጫ መስፈርት በተጨማሪ በሚያቀርበው የሴት ዕጩ ተወዳዳሪዎች ብዛት 20 በመቶ የአየር ሰዓት ድልድል እንዲኖር ውይይት ተካሂዷል።

Ethiopian Election 2021

Source: Getty Images

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ቅስቀሳ የአየር ሰአት ድልድል መመሪያ ላይ ከፖለቲካ ፓርቲዎች እና ሚዲያዎች ጋር ውይይት አድርጓል፡፡

በውይይቱ የአየር ሰአት ድልድል ቀመር፣ ድልድሉ ከዚህ በፊት የተካሄደበት መንገድ እና የድልድሉ ማከናወኛ ቴክኖሎጂ በቦርዱ እና በኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን አማካኝነት እንደቀረቡም ቦርዱ አስታውቋል።

በውይይቱም ከዚህ ቀደም በፓርላማ መቀመጫ ያለው ፓርቲ የሚያገኘው የአየር ሰአት ከ60 በመቶ ወደ 5 በመቶ እንዲቀንስ መደረጉ የውድድሩን ሜዳ የተሻለ እንደሚያደርገው የፓርቲዎች ተወካዮች ገልጸዋል ብሏል ቦርዱ፡፡

ለአየር ሰአት ድልድሉ ከፓርላማ መቀመጫ መስፈርት በተጨማሪ፡

- በእኩል የሚደለደል 25 በመቶ

- ፓርቲው በሚወዳደርበት የፌደራል እና/ወይም የክልል ም/ቤቶች በሚያቀርባቸው እጩዎች ብዛት የሚደለደል- 40 በመቶ

-  ፓርቲው በሚያቀርበው የሴት እጩ ተወዳዳሪዎች ብዛት የሚደለደል 20 በመቶ

- ፓርቲው በሚያቀርበው የአካል ጉዳተኛ እጩዎች ብዛት የሚደለደል 10 በመቶ መሆኑ ላይ ውይይት ተደርጓል ሲል ቦርዱ ገልጿል፡፡

 


Share

Published

By Stringer Report

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
በፓርላማ መቀመጫ ያለው ፓርቲ የሚያገኘው የምረጡኝ ቅስቀሳ የአየር ሰአት ከ60 በመቶ ወደ 5 በመቶ እንዲቀንስ ሃሳብ ቀረበ | SBS Amharic