በፓርላማ መቀመጫ ያለው ፓርቲ የሚያገኘው የምረጡኝ ቅስቀሳ የአየር ሰአት ከ60 በመቶ ወደ 5 በመቶ እንዲቀንስ ሃሳብ ቀረበ

*** ተወዳዳሪ ፓርቲው ከፓርላማ መቀመጫ መስፈርት በተጨማሪ በሚያቀርበው የሴት ዕጩ ተወዳዳሪዎች ብዛት 20 በመቶ የአየር ሰዓት ድልድል እንዲኖር ውይይት ተካሂዷል።

Ethiopian Election 2021

Source: Getty Images

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ቅስቀሳ የአየር ሰአት ድልድል መመሪያ ላይ ከፖለቲካ ፓርቲዎች እና ሚዲያዎች ጋር ውይይት አድርጓል፡፡

በውይይቱ የአየር ሰአት ድልድል ቀመር፣ ድልድሉ ከዚህ በፊት የተካሄደበት መንገድ እና የድልድሉ ማከናወኛ ቴክኖሎጂ በቦርዱ እና በኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን አማካኝነት እንደቀረቡም ቦርዱ አስታውቋል።

በውይይቱም ከዚህ ቀደም በፓርላማ መቀመጫ ያለው ፓርቲ የሚያገኘው የአየር ሰአት ከ60 በመቶ ወደ 5 በመቶ እንዲቀንስ መደረጉ የውድድሩን ሜዳ የተሻለ እንደሚያደርገው የፓርቲዎች ተወካዮች ገልጸዋል ብሏል ቦርዱ፡፡

ለአየር ሰአት ድልድሉ ከፓርላማ መቀመጫ መስፈርት በተጨማሪ፡

- በእኩል የሚደለደል 25 በመቶ

- ፓርቲው በሚወዳደርበት የፌደራል እና/ወይም የክልል ም/ቤቶች በሚያቀርባቸው እጩዎች ብዛት የሚደለደል- 40 በመቶ

-  ፓርቲው በሚያቀርበው የሴት እጩ ተወዳዳሪዎች ብዛት የሚደለደል 20 በመቶ

- ፓርቲው በሚያቀርበው የአካል ጉዳተኛ እጩዎች ብዛት የሚደለደል 10 በመቶ መሆኑ ላይ ውይይት ተደርጓል ሲል ቦርዱ ገልጿል፡፡

 


1 min read

Published

By Stringer Report


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now