የእንግሊዝና ኢራን ግጥሚያ በርካታ ግቦች የተቆጠሩበት ቢሆንም ለአሸናፊነት ለመብቃት ብርቱ ፍልሚያ መታየት የጀመረው የመጀመሪያው አጋማሽ ላይ ዘግየት ብሎ ነው።
ግብ ማስቆጠር ሲጀመር ግና በመጀመሪያው አጋማሽ ጨዋታ በ11 ደቂቃዎች ውስጥ ሶስት ግቦች ተቆጥረዋል።
በሁለተኛው አጋማሽም ፍልሚያው ጠንክሮ፤ ጥቃቱ በርትቶ ታይቷል።
የግጥሚያው ጠቅላላ ውጤትም እንግሊዝ 6 ኢራን 2 ግቦችን በማስቆጠር ተጠናቅቋል።
ለእንግሊዝ ቡካዮ ሳካ ለእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ሁለት ግቦችን አስቆጥሯል።

ምንም እንኳ ኢራን 6 ለ 2 በእንግሊዝ ብትረታም፤ የኢራኑ አሰልጣኝ ካርሎስ ከሮሽ የእንግሊዝ ቡድን በርትቶ በመጫወት ለድል መብቃቱን ጠቅሰው፤ የራሳቸውንም ተጫዋቾች በአዋኪ ሁኔታ ብርቱ ፍልሚያ ማድረግ እንደቻሉና በሚቀጥሉት ሁለት ግጥሚያዎች የተሻለ ውጤቶችን ማስመዝገብ እንደሚችሉ ተናግረዋል።

