“ፍትህ ለተፈጥሮ!” -- የተፈጥሮ ተቆርቋሪዋ ሀሳብና ተሞክሮ!

ተቋማትና ግለሰቦች ለተፈጥሮ ደህንነት ትኩረት እንዲሰጡ የግንዛቤ ማሳደጊያ ስራዎች ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባ የአካባቢ ተቆርቋሪዋ ሬጂና ስትሮንግ አሳስበዋል፡፡ በአሜሪካ በአካባቢ ደህንነት ተቋቋሪነታቸው የሚታወቁትና በሚችጋን የአካባቢ፣ሀይቆችና ኢነርጂ ክፍል የሚሰሩት ሬጂና ስትሮንግ ይህን ማሳሰቢያ የሰጡት በአየር ንብረት ለውጥና አካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ላይ አተኩረው ከሚሰሩ ጋዜጠኞች ጋር ሲወያዩ ነው፡፡

Ceara Carney

Extinction Rebellion activists, Ceara Carney dresses blindfolded in a gown as Lady Justice in Dublin to show the the injustice of climate inaction. Source: Getty

“ፍትህ ምንድነው” በሚል ጥያቄ መነሻ ስለፍትህ ማብራሪያ የጀመሩት ስትሮንግ፤ ስለእኩልነት ብቻ ሳይሆን ስለፍትሀዊነት ማሰብ አለብን ብለዋል፡፡ የዓለም ማህበረሰብ በተፈጥሮ መጎዳት ከፍተኛ ተጽዕኖ እየደረሰበት መሆኑን ሬጂና ስትሮንግ አጥብቀው ይናገራሉ፡፡

ከሰው ልጅ አኗኗር ጋር በተገናኘ በተፈጥሮ ላይ ጉዳት እየደረሰ በመሆኑ እየደረሰ ስላለው ጉዳትና አጥፊዎች ላይ መወሰድ ስላለበት እርምጃ በትኩረት መታሰብ አለበት ብለዋል፡፡
Regina Strong.
Regina Strong. Source: Zoom Meeting
የአካባቢ ተቆርቋሪዋ ሬጂና የተፈጥሮ እንክብካቤ ሃሳብን ለማስረጽና ለውጥ እንዲመጣ የአስተሳሰብ ችግር መቀረፍ የሚገባው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በተለይ ለተፈጥሮ ፍትህን መጠየቅ አዲስ ሀሳብና እንግዳ ስለሆነ የእኛን አስተሳሰብ ለሌላው ማስገንዘቡ ፈተና ነው ብለዋል፡፡ በመንግስት አሰራር ዘንድም በተለመደው ሂደት የመጓዝ አዝማሚያም እንደዋና ችግር መታየት እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ በበርካታ አገራት የሚስተዋለው ስለ ተፈጥሮ ደህንነት የመንግስት አሰራርና መረጃ ውሸት የበዛበትና ረጅም ጊዜ የሚወስድ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ለረጂም ዓመታት በተቆርቋነትና በተፈጥሮ ጉዳዮች አስተሳሰብ ለመቅረጽ ሲሰሩ የቆዩት ሬጂና ስትሮንግ አሁን በሚችጋን የአካባቢ፣ሀይቆችና ኢነርጂ ክፍል በመንግስት መዋቅር እየሰሩ መሆኑን ይገልጻሉ፡፡ በሚሰሩበት ሚችጋን የአካባቢ፣ ሀይቆችና ኢነርጂ ክፍል መቋቋሙ በራሱ ትልቅ እምርታ እንደሆነም ያምናሉ፡፡ በአካባቢው ካሉት የመንግስት ሃላፊዎች ጋር በአካባቢ ጉዳዮችና ሀይቆች ጥበቃ ዙሪያ በቁርኝት እንደሚሰሩም ተናግረዋል፡፡

ሬጂና ስትሮንግ በሚሰሩበት ክፍል በዋናነት የአስተሳሰብ ለውጥ እንዲመጣ እየሰሩ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡ በሁለት ዓመት ውስጥ ለተፈጥሮ ፍትህን ማረጋገጥ እንዲቻል ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ትኩረት እንደተሰጠ ገልጸዋል፡፡ በተለይ የመንግስት ሰራተኞች ስለአካባቢ ደህንነትና ለተፈጥሮ ፍትህ መረጋገጥ ዓለምአቀፍ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ስልጠና እየሰጡ መሆናቸውን ነው የሚናገሩት፡፡ በዚህም 49ኛው የሚችጋን ገዢ ዊትሜር ሁሉም ሰራተኞች ስልጠና እንዲወስዱ ማዘዛቸውንም  አስታውሰዋል፡፡
Regina Strong.
Source: Zoom Meeting
መንግስት በመሰል ስራዎች የመሳተፉን አስፈላጊነት አስመልክቶ ለተነሳላቸው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት ሬጂና ስትሮንግ የተፈጥሮ ፍትህ መዛባት የሚስተካከለው በመንግስት ተሳትፎ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡ “መቀየር ያለባቸውን ህጎችና መፍትሄዎች በውይይትና በምክክር ለመቀየር እንሰራለን፤ መንግስት በፍትሃዊ መፍትሄዎች መሳተፍ አለበት፡፡ በየደረጃው ያለው መንግስት አካል እና በዋናነት ከከባቢ ብክለት ስማቸው የሚነሳው ባለኢንዱስትሪዎች ለተፈጥሮ ፍትህን በማረጋገጡ ሂደት በግንባርቀደምትነት መሳተፍ ይገባቸዋል” ብለዋል፡፡

በታዳጊ ሀገራት የኢንቨስትመንት ፈቃድ ለሚወስዱ ኢንቨስተሮችም አስቀድሞ በአካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች የቁጥጥርና ክትትል ስርአት መዘርጋት እንዳለበት የገለጹት ሬጂና ስትሮንግ ይህም እንዲተገበር ማህበረሰቡና መንግስት ለአካባቢ ደህንነት ጉዳዮች ትኩረት በመስጠት በጋራ መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡

አሁን ባለንበት የኮሮና ዘመን የሀይል አቅርቦትን በተመለከተ በተለይ ለድሃው ማህበረሰብ ድጋፍ ታደርጋላችሁ ወይ በሚል ለተነሳላቸው ጥያቄ ትኩረት የሰጠነው በሁሉን አቀፍ መንገድ እንዴት ለማህበረሰቡ እንድረስና ምን እናቅርብ ለሚለው ሀሳብ ነው ብለዋል፡፡

አሜሪካ በተለይ የአረንጓዴ ህጎችን በተመለከተ ስላላት ተሞክሮና አተገባበር ሀሳብ እንዲሰጡ ከጋዜጠኞች የተጠየቁት የተፈጥሮ ተቋርቋሪዋ ሚችጋንን ምሳሌ በማድረግ ህግ አውጭዎች ጋር ሙከራዎች እንዳሉና መሻሻል ያለባቸው ብዙ ጉዳዮች እንዳሉ አንስተዋል፡፡ ህግ አውጪና ህግ አስፈጻሚ አካላት ላይ ክትትል እንደሚያደርጉም አረጋግጠዋል፡፡
Regina Strong.
Regina Strong (L) and Gretchen Esther Whitmer (R). Source: Zoom Meeting
የተፈጥሮን ክብካቤ በተለያዩ ጊዜያት የማህበረሰብ ንቃት ለመፍጠር በሚንቀሳቀሱ ወቅት ከህግ በላይ ሁነው የተፈጥሮን መብት የሚጥሱ እንደሚገጥሟቸው የተናገሩት ሬጂና ስትሮንግ ቢሆንም ግን ተስፋ መቁረጥ እንደማይገባ ይናገራሉ፡፡ “አሁንም አሁንም ማስተማር ማስተማር ማስተማር ይገባል” ነው የሚሉት፡፡

ሚዲያዎች እውነተኛ ታሪኮችን ለሰው ልጆች መንገር እንዳለባቸው ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ወደፊት ለሚያራምዱ ታሪኮች ትኩረት መደረግ እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡ “ትኩረት ሁሉ ለፍትህ … ለምድር… ለተፈጥሮና … ለሰው ልጆች” ብለዋል፡፡

 

ደመቀ ከበደ

 

 


Share

Published

By Demeke Kebede

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service