ኢትዮጵያ ግማሽ ትሪሊዮን ብር በጀት አፀደቀች

*** በ2014 ዓ.ም ከተያዘዉ በጀት መካከል መንገድ 67.45 ቢሊየን፤ ትምህርት 66.06 ቢሊየን ፤ ዕዳ ክፍያ 45.12 ፤ መከላከያ 22.00 ቢሊየን ብር እና ጤና 20.43 ቢሊየን ብር የተመደበላቸው ቀዳሚ ሴክተሮች ሆነዋል።

SBS Amharic

Source: SBS Amharic

ዛሬ ጠዋቱን በተከናወነው የ6ተኛው የስራ ዘመን 4ተኛ ልዩ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ የ2014 የኢትዮጵያ ዓመታዊ በጀት 561.7 ቢሊየን ብር ሆኖ ፀድቋል።

በጀቱ 162.17 ቢሊየን ብሩ ለመደበኛ ወጭ፤ 183.55 ቢሊየኑ ለካፒታል ወጭ ፤ 203.95 ቢሊየን ለክልሎች ድጋፍ እንዲሁም 12.00 ቢሊየን ለዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈጸሚያ ይውላል፡፡

Budget 2014.
Source: Ethiopian Parliament

የ2014 የፌደራል መንግስት ጠቅላላ ገቢ ከታክስ 334.01 ፤ ታክስ ካልሆኑ 35.10 እንዲሁም መሰረታዊ አገልግሎት ከለላ እርዳታ 38.75 እና ፕሮጀክት እርዳታ 28.06 ቢሊዮን እንደሚሰበሰብ ተገልጿል፡፡

Budget 2014.
Source: Ethiopian Parliament

በ2014 ዓ.ም ከተያዘዉ በጀት መካከል መንገድ 67.45 ቢሊየን፤ ትምህርት 66.06 ቢሊየን ፤ ዕዳ ክፍያ 45.12 ፤ መከላከያ 22.00 ቢሊየን ብር እና ጤና 20.43 ቢሊየን ብር የተመደበላቸው ቀዳሚ ሴክተሮች ሆነዋል።

[ ደመቀ ከበደ ፡ አዲስ አበባ ]


1 min read

Published

By Demeke Kebede


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now