ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የምርጫ አሸናፊ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አሳወቀ

*** የቀድሞው የአብን ሊቀ መንበር ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔም ድል ቀንቷቸዋል

Solyana Shimelis, spokeswoman of the National Electoral Board of Ethiopia.

Solyana Shimelis, spokeswoman of the National Electoral Board of Ethiopia. Source: Demeke Kebede

የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንት አብይ አህመድ ( ዶር ) ለፌደራሉ ተወካዮች ምክር ቤት በተወዳደሩበት የጎማ 2 ምርጫ ጣቢያ ማሸነፋቸውን ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።

ከዶር አብይ ጋር የተወዳደሩት ከእናት ፓርቲ አቶ ዳግም ዋሪሶ እና ከኢዜማ ደግሞ ካሊድ ጀማል ናቸው።

ቦርዱ እንዳስታወቀው ዶር አብይ በከፍተኛ ድምጽ ብልጫ ያሸነፉ ሲሆን በምርጫ ክልሉ ከተሰጠው 79 ሺህ 295 ድምጽ ውስጥ ዐቢይ 76 ሺህ 892 ድምጽ አግኝተዋል ብሏል።

በተመሳሳይ በአማራ ክልል ባሕር ዳር ምርጫ ክልል የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ ፡ አብን የሥራ አስፈጻሚ አባል እና የቀድሞው የፓርቲው ሊቀመንበር ዶር ደሳለኝ ጫኔ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ ማሸነፋቸውን ቦርዱ አክሎ ገልጿል።

ቦርዱ በዛሬው መግለጫው ሁሉም የምርጫ ውጤቶች ወደ ዋና መስሪያ ቤቱ እንደደረሱለት አረጋግጧል። እያጣራ ውጤቶችን እንደሚያሳውቅም የኮሙኒኬሽን ኃላፊዋ ወይዘሪት ሶልያና ሽመልስ ተናግረዋል።


[ ደመቀ ከበደ ፡ አዲስ አበባ ]


Share

Published

By Demeke Kebede

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service