የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ዶር ዐቢይ አሕመድ የነገውን የምርጫ ቀን አስመልክቶ ዛሬ ከብሔራዊ ምርጫ ደህንነት ስትራቴጂ ማዘዣ ጋር እንደተወያዩ በማህበራዊ ትስስር ገፆቹ ገልጿል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት በማዕከላዊ ዕዝ የሁኔታ ክትትል ክፍል ውስጥ ይፋ የተደረገው የብሔራዊ መረጃና ደህንንነት አገልግሎት የምርጫ ደህንነት መድረክ በምርጫ ደህንነት ዘርፍ የተከናወነውን ዝግጁነት እንደገመገመ ነው የተገለፀው።
" የደህንነቱ ዝግጁነት በሁሉም የሀገሪቱ ማእዘናት ላይ አካላዊ ኃይል ማሰማራትን እንዲሁም የሳይበር ደህንነት ማሻሻያዎችን የተመለከቱ ስጋቶችን ማክሸፍን ያጠቃልላል።" ብሏል ጽህፈት ቤቱ ያወጣው መግለጫ
በመግለጫው እንደተጠቀሰው "በመላው የፌዴራል እና የክልል ማዘዣ ጣቢያዎች ባሉ የመረጃ መጋራት መሳሪያዎች፣ የሳተላይት ቁጥጥር ስርዓቶች እና የድሮን ቴክኖሎጂ ለዚሁ ዝግጅት ተሰማርተዋል" ተብሏል።

Election security meeting Source: PMOE
በመግለጫው ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ " ይህንን አዲስ አካሄድና ከብሔራዊ ቁልፍ ተግባራት ቀድሞ ብሔራዊ ደህንነትን በማረጋገጥ ረገድ የተፈጠረውን አቅም " እንደተመለከቱ ተገልጿል።
በምርጫው ወቅት ሊያጋጥሙ ስለሚችሉ የፀጥታ ስጋቶችና አጠቃላይ የቦርዱን ዕቅድ አፈፃፀም በተመለከተ ከሰሞኑ በጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ከ ኤስ ቢ ኤስ አማርኛ ዘጋቢ ለቀረበ ጥያቄ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ወይዘሪት ሶልያና ሽመልስ በእስካሁን የቦርዱ ምልከታና ከፀጥታ ተቋማት ካገኙት መረጃ እንደተገነዘቡት የምርጫ ሂደቱን ሊያውክ የሚችል ጉልህ የፀጥታ ችግር ሊያጋጥም እንደማይችል እምነታቸው መሆኑን መናገራቸው ይታወሳል።
[ ደመቀ ከበደ ፡ አዲስ አበባ ]