የድምፅ መስጫ ቀን መስሪያ ቤቶች ዝግ እንዲሆኑ መወሰኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ

*** በምርጫው ቀን ሁሉም የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ዝግ ሲሆኑ፤ ይህንኑም ለማካካስ ቅዳሜ ዕለት ወደ ሥራ ገበታቸው ይመለሳሉ

Solyana Shimeles

Spokesperson of the National Election Board of Ethiopia (NEBE) Solyana Shimeles . Source: Getty

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ወይዘሪት ሶልያና ሽመልስ እንደገለፁት ሰኞ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም የድምፅ መስጫ ቀን በመሆኑ በእለቱ የተመዘገቡ ዜጎች ሁሉ ድምጻቸውን ለመስጠት ይችሉ ዘንድ እና የደምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ያለምንም የጸጥታ ችግር ይከናወን ዘንድ መስሪያ ቤቶች እንዲዘጉ ተወስኗል ብለዋል።

ሶልያና እንዳሉት የምርጫ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና ስነምግባር አዋጅ 1162/ 2011 አንቀጽ 161 የመተባበር ግዴታ መሰረት ለመንግስታዊ እና ለማንኛውም መንግስታዊ ላልሆኑ ተቋማት ተግባራዊ  መደረግ እንደሚገባው ጠቅሰዋል።

በዚህ መሰረት ዜጎች ዕለቱን ለድምጽ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ የፌዴራል እና የክልል ( ከሃረሪ እና ከሶማሌ ክልል ውጪ) መንግስታዊ ተቋማት ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ስራ ዝግ እንዲያደርጉ ፣ ዜጎች እለቱን ለድምጽ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ በክልሎች (ከሃረሪ እና ከሶማሌ ክልል ውጪ) እና በፌዴራል የሚገኙ ማንኛውም መንግስታዊ ያልሆኑ እና የግል ተቋማት በተመሳሳይ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዝግ እንዲያደርጉ ተወስኗል።

 ይሁንና የአስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት፣ ሆስፒታሎች፣ የዕለት ተዕለት አገልግሎት ሰጪዎችም (ሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች፣ የትራንስፓርት አገልግሎት..) በዝግ ቀናት የሚያደርጉትን አገልግሎት በተመሳሳይ የሚያከናውኑ ሲሆን የመተባበር ግዴታው እነዚህን ተቋማት እንቅስቃሴ መዘጋት አያስገድድም ተብሏል።

 ቦርዱ ባወጣው መግለጫ እንደተጠቀሰው የትራንስፖርት አገልግሎት በተለመደው መንገድ የሚቀጥል ቢሆንም ዜጎች ድምጽ ከመስጠት ውጪ ከፍተኛ እንቅስቃሴን የሚፈልጉ ሁነቶችን እና እቅዶችን እንዳይይዙ እና እንቅስቃሴያቸውን ድምጽ ለመስጠት ብቻ እንዲያደርጉ ቦርዱ ጠይቋል።

በሌላም በኩል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በምርጫው ዕለት ዝግ እንደሚሆኑ ሲያስታውቁ "ሁሉም የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በዕለቱ ዝግ ይሆናሉ። እሱንም ለማካካስ ቀጥሎ በሚመጣው ቅዳሜ ወደ ሥራ የምንገባ ይሆናል" ብለዋል። 

[ ደመቀ ከበደ ፡ አዲስአበባ ]


Share

Published

By Demeke Kebede

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
የድምፅ መስጫ ቀን መስሪያ ቤቶች ዝግ እንዲሆኑ መወሰኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ | SBS Amharic