የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን የመጀመሪያ ግኝት ሪፖርት

*** በቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝደንት ኦሊሴጎን ኦባሳንጆ የተመራው የአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን የኢትዮጵያ ምርጫ በተመለከተ የመጀመሪያውን ግኝት ሪፖርቱን ረቡዕ ጁን 23 በስካይ ላይት ሆቴል ይፋ አድርጓል።

Chief Olusegun Obasanjo

Chief Olusegun Obasanjo, Head of AUEOM, Ethiopia 2021 General Election, Former Pesident of Nigeria. Source: SBS Amharic/Demeke Kebede

በ5 ክልሎች እና 2 ከተሞች ምርጫውን መታዘቡን ያስታወቀው ታዛቢ ልዑኩ በዘጠኝ ገፅና በ13 አንኳሮች ባዋቀረው ሪፖርቱ ይፋ እንዳደረገው " ምርጫው በብዙ መልኩ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ መስፈርቶችን ያሟላና ዴሞክራሲያዊ ነው።" ብሏል።

ምርጫ ቦርዱንም " ግልፅና አሳታፊ ሂደት በመተግበሩ " ያደነቀ ሲሆን የቀድሞዋ ፖለቲከኛና ዳኛ ብርቱካን ሚዴቅሳን ለዚህ የጎላ ሚና እንደተጫወቱ ጠቅሷል። "ምርጫ ቦርዱ ሙያዊና ነፃነቱን የተላበሰ ለመሆን ያደረገውን ተቋማዊ ጥረት ያየንበት ነው " ሲልም መስክሯል።

በምርጫው 53 ፓርቲዎች ተመዝግበው 46ቱ ዕጩዎቻቸውን ለውድድር ማቅረባቸውን ከእነዚህም 17 ያህል ለፌደራል እንዲሁም 29 ኙ ደግሞ ለክልል መወዳደራቸውን እንዳረጋገጠ ጠቅሷል።

የተመረጡ ጣቢያዎች ላይ ምልከታ አድርገናል ያሉት የሪፖርቱ አቅራቢ ኦሊሴንጎ ኦባሳንጆ  "ምርጫውን ተዘዋውረን በተመለከትንበት የምርጫ ቦርድን ተቋማዊ ጥንካሬ ተመልክተናል፣ መንግስት ምርጫው ሰላማዊ እንዲሆን አስፈላጊ የጸጥታ እርምጃ ተግባራዊ አድርጓል" ብለዋል። "ድምጽ ሰጪዎች በምርጫው ደስተኛ መሆናቸውንና የፈለጉትን በነጻነት መምረጣታቸውን ነግረውኛል። የመራጮቹ ትዕግስትም አስገራሚ ነበር" ሲሉ አክለዋል።

"ምርጫው ከሞላ ጎደል ሰላማዊ በሆነ መልኩ ነው የተካሄደው። በአንዳንድ ቦታዎች በተለይም በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች ከጸጥታ ጋር ተያይዞ ስጋቶች እና በአንዳንድ ምርጫ ጣቢያዎች የተቃዋሚ ፓርቲ ወኪሎችን የማዋከብ እና የማንገላታት ችግሮች መስተዋሉን" ኦባሳንጆ ገልፀዋል። "የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ መንግስት እና የጸጥታ አካላት ስራቸውን በአግባቡ ቢሰሩም የቁሳቁስ እጥረትና የመራጮች ብዛት በድምጽ አሰጣጡና በቆጠራው ሂደት ላይ ጫናን ፈጥሯል"  ሲሉ ቡድናቸው ያስተዋላቸውን እንከኖች ተናግረዋል የልዑኩ መሪ ኦባሳንጆ።

የሲቪክ ማህበረሰብ አካላት በምርጫው የሚያደርጉትን ተሳትፎ መቀጠልና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ተቋማትን ለማጠናከር የሚያደርጉትን ድጋፍ እንዲያጠናክሩ ኦባሳንጆ ጠይቀዋል።

የአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክ የትዝብቱን የተጠቃለለ ሪፖርት ከ2 ወራት በኋላ ይፋ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።

[ ደመቀ ከበደ ፡ አዲስ አበባ ]


Share

Published

Updated

By Demeke Kebede

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service