የመራጩ ሕዝብ ተሳትፎ ለቦርዱ አመኔታ የሰጠ ነው ብሎ እንደሚያምን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ገለጠ

*** ትናንት የምርጫ አስፈፃሚዎቹ የፀጥታ ስጋት አለብን በሚል የተዘጋው በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ አምቦ የሚገኝ ምርጫ ጣቢያ እስካሁን አልተከፈተም

Solyana Shimelis

Solyana Shimelis, spokeswoman of the National Electoral Board of Ethiopia. Source: Demeke Kebede

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ሶልያና ሽመልስ አሁን በሰጡት መግለጫ እንዳሉት በአዲስ አበባም ሆነ በክልሎች የታየው የመራጩ ህዝብ ተሳትፎ የላቀ እንደነበርና ይህም ቦርዱን በትክክል ድምፄን ይቆጥርልኛል የሚል እምነት እንዳሳደረ የሚያሳይ ነው ብለዋል። ሶልያና ድምፅ የሰጠውን ህዝብ ቁጥር ከየስፍራው አደራጅተው በቅርቡ እንደሚያሳውቁ የገለፁ ሲሆን በትናንትናው ዕለት በተለያዩ አካባቢዎች ቦርዱ ባደረገው ቅኝት ረጅም ሰልፎች ከጠዋት እስከ ምሽት ድረስ መታዘባቸውን ገልፀው በዚህም ቦርዱ ለቀጣይ ስራው ብርታት ሆኖታል ፡ ተዓማኒ ተቋም ለመመስረት የምናደርገውን ጥረት የሚያጎላ ነው ብለዋል።

ሶልያና አብዛኞቹ የምርጫ ጣቢያዎች ውጤት መግለፅ እንደጀመሩም ለጋዜጠኞች አረጋግጠዋል። ይሁንና የምርጫ ጣቢያዎች ውጤት እንጅ የምርጫ ክልሎች ውጤቶች ገና በመገለፅ ላይ ባለመሆናቸው የጣቢያዎቹን ድምር በራሳቸው አስልተው እየገለፁ ያሉ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ በአፅንኦት አሳስበዋል።

ሶልያና እንዳሉት የምርጫ ክልሎች ውጤቶች የሚታወቁት ምርጫ ጣቢያዎቹ ለየአቅራቢያዎቻቸው የምርጫ ክልሎች ልከው ከተደመረ በኋላ ሲሆን ገና ቆጠራዎች ያልተጠናቀቁባቸው ጥቂት ጣቢያዎች ያሉ በመሆናቸውና ብዙዎቹም ውጤቶቻቸውን በየጣቢያዎቻቸው ቢያሳውቁም ለምርጫ ክልሎቹ ገና እየላኩ በመሆናቸው የአሸናፊዎች ውጤት እንደታወቀ ተደርጎ መነገሩ ህዝብን ለመረጃ መምታት ያጋልጣል፣ ይህ ሊቆም ይገባል ብለዋል።

በሌላ በኩል ትናንት የምርጫ አስፈፃሚዎቹ የፀጥታ ስጋት አለብን በሚል የተዘጋው በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ አምቦ የሚገኝ ምርጫ ጣቢያ እስካሁን አልተከፈተም ብለዋል። በዚህ ጉዳይ የቦርዱ ውሳኔ ምንድን ነው በሚል ከSBS ዘጋቢ የተጠየቁት ሶልያና አሁንም ቁሳቁሶቹ ታሽገው እንደተዘጋባቸው ሲሆን ቦርዱ በቅርቡ ውሳኔውን ያሳውቃል ብለዋል።

በሲዳማ 19 ምርጫ ክልሎች  እየተካሄደ ያለው ምርጫም በብዙዎቹ ጣቢያዎች ተጠናቋል ያሉ ሲሆን ቀሪዎቹም በሰዓቱ እንደሚጠናቀቅ ተናግረዋል። በተመሳሳይ በጋምቤላ አራት ምርጫ ጣቢያዎችም ድምፅ ሲሰጥ መዋሉን ገልፀዋል።

ትናንት በራዲሰን ብሉ ሆቴል ህይወታቸው ስላለፈው ዓለም አቀፍ " ታዛቢ " ጉዳይ ቦርዳቸው ስላለው አስተያየት ተጠይቀው በህልፈታቸው ቦርዳቸው ማዘኑን ገልፀው ግለሰቡ የምርጫ ታዛቢ ሳይሆኑ " የክብር እንግዳ ( Guest ) " ነበሩ ብለዋል።

ደመቀ ከበደ ፡ አዲስ አበባ


Share

Published

By Demeke Kebede

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service