በጥሞና ወቅት የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ቃለ መጠይቅ እንዳይተላለፍ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኅን ባለስልጣን አሳሰበ

*** በማኅበራዊ ሚዲያዎች እየተላለፉ ያሉ የምርጫ ቅስቀሳ የሚመስሉ መልዕክቶችም እንዲቆሙ ተጠይቋል

Abiy Ahmed, Ethiopia's prime minister.

Abiy Ahmed, Ethiopia's prime minister. Source: Getty

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ሰሞኑን ለመገናኛ ብዙሃን  የሰጡት ቃለ መጠይቅ በዚህ በጥሞና ወቅት በመገናኛ ብዙሃን እንዳይተላለፍ ሲል የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሀን ባለስልጣን አሳሰበ።

በማሕበራዊ ሚዲያዎች እየተላለፉ ያሉ የምርጫ ቅስቀሳ የሚመስሉ መልዕክቶችም መቆም አለባቸው ብሏል።

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ እድሪስ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ምንም እንኳን ቃለ መጠይቁ የመንግስት የስራ ክንውኖች ላይ ያተኮረና የምርጫ ቅስቀሳ እንዳልሆነ ቢታወቅም በዚህ ጥሞና ወቅት ሊተላለፍ አይገባም።

የቃለ መጠይቁ መተላለፍ ብዥታ እንዳይፈጥር ሲባል ከምርጫው በፊት መተላለፍ እንደሌለበት አቶ መሀመድ አስታውቀዋል።

በተጨማሪም ቃለ መጠይቁ እንዳይተላለፍ የተፈለገው መንግስት በዚህ ዓመት የተሻለ ምርጫ እንዲካሄድና ፍትሀዊ  እንዲሆን ፍላጎት ስላለው መሆኑን ተናግረዋል።

ስለዚህ ቃለ መጠይቁን ለማስተላለፍ ማስታወቂያ እየሰሩ ያሉ መገናኛ ብዙሃንም ሆኑ ለማስተላለፍ የተዘጋጁ ከወዲሁ እንዲያቆሙ አሳስበዋል።

በተመሳሳይ የማሕበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም የምርጫ ቅስቀሳ የሚመስሉ መልዕክቶችን እያስተላለፉ ያሉ አካላትም ከድርጊታቸው መታቀብ አለባቸው ብለዋል።

መገናኛ ብዙሃንም ቢሆኑ የምርጫ ቅስቀሳ ወቅት በመጠናቀቁ ቅስቀሳ መሰል ዘገባዎችን ከማስተላለፍ ሊጠነቀቁ ይገባል ብለዋል።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሀን ባለስልጣን ባወጣው የሰዓት ድልድል መሰረት የፖለቲካ ፓርቲዎች መገናኛ ብዙሃንን ተጠቅመው የተሳካ ቅስቀሳ ሲያደርጉ መቆየታቸውንም አስታውሰዋል።

[ENA]


Share

Published

By Stringer Report

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service