በጥሞና ወቅት የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ቃለ መጠይቅ እንዳይተላለፍ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኅን ባለስልጣን አሳሰበ

*** በማኅበራዊ ሚዲያዎች እየተላለፉ ያሉ የምርጫ ቅስቀሳ የሚመስሉ መልዕክቶችም እንዲቆሙ ተጠይቋል

Abiy Ahmed, Ethiopia's prime minister.

Abiy Ahmed, Ethiopia's prime minister. Source: Getty

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ሰሞኑን ለመገናኛ ብዙሃን  የሰጡት ቃለ መጠይቅ በዚህ በጥሞና ወቅት በመገናኛ ብዙሃን እንዳይተላለፍ ሲል የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሀን ባለስልጣን አሳሰበ።

በማሕበራዊ ሚዲያዎች እየተላለፉ ያሉ የምርጫ ቅስቀሳ የሚመስሉ መልዕክቶችም መቆም አለባቸው ብሏል።

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ እድሪስ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ምንም እንኳን ቃለ መጠይቁ የመንግስት የስራ ክንውኖች ላይ ያተኮረና የምርጫ ቅስቀሳ እንዳልሆነ ቢታወቅም በዚህ ጥሞና ወቅት ሊተላለፍ አይገባም።

የቃለ መጠይቁ መተላለፍ ብዥታ እንዳይፈጥር ሲባል ከምርጫው በፊት መተላለፍ እንደሌለበት አቶ መሀመድ አስታውቀዋል።

በተጨማሪም ቃለ መጠይቁ እንዳይተላለፍ የተፈለገው መንግስት በዚህ ዓመት የተሻለ ምርጫ እንዲካሄድና ፍትሀዊ  እንዲሆን ፍላጎት ስላለው መሆኑን ተናግረዋል።

ስለዚህ ቃለ መጠይቁን ለማስተላለፍ ማስታወቂያ እየሰሩ ያሉ መገናኛ ብዙሃንም ሆኑ ለማስተላለፍ የተዘጋጁ ከወዲሁ እንዲያቆሙ አሳስበዋል።

በተመሳሳይ የማሕበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም የምርጫ ቅስቀሳ የሚመስሉ መልዕክቶችን እያስተላለፉ ያሉ አካላትም ከድርጊታቸው መታቀብ አለባቸው ብለዋል።

መገናኛ ብዙሃንም ቢሆኑ የምርጫ ቅስቀሳ ወቅት በመጠናቀቁ ቅስቀሳ መሰል ዘገባዎችን ከማስተላለፍ ሊጠነቀቁ ይገባል ብለዋል።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሀን ባለስልጣን ባወጣው የሰዓት ድልድል መሰረት የፖለቲካ ፓርቲዎች መገናኛ ብዙሃንን ተጠቅመው የተሳካ ቅስቀሳ ሲያደርጉ መቆየታቸውንም አስታውሰዋል።

[ENA]


1 min read

Published

By Stringer Report


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now