የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ ምርጫው ከዘጠኝ እስከ 12 ወራት እንዲራዘም ከመጨረሻ የውሳኔ ሃሳቡ ላይ ደረሰ

የኢፌዴሪ የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የደረሰውን የሕገ መንግሥቱን አንቀጽ 54(1)፣ 58 (3) እና 93ን የመተርጎም ጥያቄ ተከትሎ የምርጫው ጊዜ ከዘጠኝ ወራት እስከ አንድ ዓመት ባሉት ጊዜያት ውስጥ እንዲራዘም ከሚል የውሳኔ መቋጫ ላይ በሙሉ ድምፅ መድረሱን ሰነዶች አመላክተዋል።

Ethiopian Constitution

Ethiopian parliament Source: Courtesy of PD

የሕገ መንግሥት አጣሪ ጉባኤው ይህንኑ የመጨረሻ የውሳኔ ሃሳቡን በዚህ ሳምንት መጨረሻ ወይም በመጪው ሳምንት መጀመሪያ ለሚታደመው ምክር ቤት እንደሚያቀርብ ይጠበቃል።

አጣሪ ጉባኤው በሙሉ ድምፅ ፅድቅ በቸረው የውሳኔ ሃሳቡ ላይ ሁለት ዋነኛ ማብራሪያና የሕገ መንግሥት ትርጓሜ ዕሳቤዎቹን አስፍሯል። 

  1. በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 54 (1)፣ 58 (3) እና 72 (3) ላይ የተደነገገው የአምስት ዓመት የሥራ ዘመን ከአንቀጽ 93 እንዲሁም ከሕገ መንግሥቱ መሠረታዊ መርሆዎች፤ ዓላማዎችና ግቦች ጋር በማገናዘብ የኮቪድ - 19 ወረርሽኝ የሕዝብ ጤና ስጋት ሆኖ ባለበትና የበሽታውን ስርጭት ለመከላከል ፣ ለመቆጣጠርና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ የወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 3/2012 ጸንቶ በሚቆይባቸው ጊዜያትና ከተነሳም በኋላ አዲስ ምርጫ ተካሂዶ የስልጣን ርክክብ እስከሚፈጸምበት ጊዜ ድረስ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ የፌዴሬሽን ምክር ቤት፣ የክልል ምክር ቤቶችና የፌዴራልና የክልል አስፈጻሚ አካላት የሥራ ዘመን እንዲቀጥል በማለት በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 84 (1) መሠረት የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት የመጨረሻ ውሳኔ እንዲሰጥበት የውሳኔ ሃሳብ አቅርቧል።
2. የኮቪድ - 19 ሥርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠርና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ የወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 3/2012 እንዲታወጅ ምክንያት የሆነው ወረርሽኝ ዓለም አቀፍና የጤና ድርጅቶች የሚያወጡትን መረጃ መሠረት በማድረግ የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር እንዲሁም የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትና የሳይንሱ ማኅበረሰብ አካላት ወረርሽኙ የሕዝብ ጤና ስጋት አለመሆኑን ካረጋገጡበትና ይህም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ ከዘጠኝ ወር እስከ አንድ ዓመት ባለው ጊዜ ውስጥ ምርጫው እንዲካሔድ በማለት በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 84 (1) መሠረት የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት የመጨረሻ ውሳኔ እንዲሰጥበት የውሳኔ ሃሳብ አቅርቧል።       


Share

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service