የኢትዮጵያ አገር መከላከያ ሠራዊት ሁለት አዳዲስ ዕዞችን መሠረተ

*** አዲስ የተደራጁት ዕዞች በ2013 ወታደራዊ ግዳጃቸው ላይ ይሰማራሉ

FRDE Defence Force

Source: PD

የኢትዮጵያ አገር መከላከያ ሠራዊት የወታደራዊ ግዳጃ አፈጻጸሙን ለማቀልጠፍ ሁለት ተጨማሪ ዕዞችን መመስረቱን በትናንትናው ዕለት በብዙኅን መገናኛ በኩል አድርጓል። 

የሁለት ተጨማሪ ዕዞችን መቋቋም በጠሩት ጋዜጣዊ መግለጫ ያስታወቁት የኢትዮጵያ አገር መከላከያ ሠራዊት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል አደም መሐመድና የሠራዊቱ የጦር ኃይሎች ምክትል ኤታማዦር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ ናቸው።

በጋዜጣዊ መግለጫው ወቅት አዲስ የተቋቋሙት ዕዞች የማዕከላዊና ሰሜን ምዕራብ ዕዞች መሆናቸው ተነግሯል።

ቀደም ሲል ተደራጅተው ያሉት የሰሜን፣ ደቡብ፣ ምዕራብና ምሥራቅ ዕዞች በአወቃቀራቸው ጸንተው ግዳጃቸውን ማከናወኑን ይቀጥላሉ።

ጄኔራል መኮንኖቹ የአገር መከላከያ ሠራዊቱን አደረጃጀት፣ የማሻሻያ ለውጥ እንቅስቃሴዎች፣ የወቅቱን የፀጥታና ሰላም ሁኔታዎች አስመልክተውም ማብራሪያ ሰጥተዋል።    


Share

Published

Updated

By Stringer

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service