የኢትዮጵያ አገር መከላከያ ሠራዊት ሁለት አዳዲስ ዕዞችን መሠረተ

*** አዲስ የተደራጁት ዕዞች በ2013 ወታደራዊ ግዳጃቸው ላይ ይሰማራሉ

FRDE Defence Force

Source: PD

የኢትዮጵያ አገር መከላከያ ሠራዊት የወታደራዊ ግዳጃ አፈጻጸሙን ለማቀልጠፍ ሁለት ተጨማሪ ዕዞችን መመስረቱን በትናንትናው ዕለት በብዙኅን መገናኛ በኩል አድርጓል። 

የሁለት ተጨማሪ ዕዞችን መቋቋም በጠሩት ጋዜጣዊ መግለጫ ያስታወቁት የኢትዮጵያ አገር መከላከያ ሠራዊት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል አደም መሐመድና የሠራዊቱ የጦር ኃይሎች ምክትል ኤታማዦር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ ናቸው።

በጋዜጣዊ መግለጫው ወቅት አዲስ የተቋቋሙት ዕዞች የማዕከላዊና ሰሜን ምዕራብ ዕዞች መሆናቸው ተነግሯል።

ቀደም ሲል ተደራጅተው ያሉት የሰሜን፣ ደቡብ፣ ምዕራብና ምሥራቅ ዕዞች በአወቃቀራቸው ጸንተው ግዳጃቸውን ማከናወኑን ይቀጥላሉ።

ጄኔራል መኮንኖቹ የአገር መከላከያ ሠራዊቱን አደረጃጀት፣ የማሻሻያ ለውጥ እንቅስቃሴዎች፣ የወቅቱን የፀጥታና ሰላም ሁኔታዎች አስመልክተውም ማብራሪያ ሰጥተዋል።    


1 min read

Published

Updated

By Stringer



Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now

የኢትዮጵያ አገር መከላከያ ሠራዊት ሁለት አዳዲስ ዕዞችን መሠረተ | SBS Amharic