የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አገር አቀፍ ምርጫ በ2013 እንዲካሔድ በአብላጫ ድምፅ ወሰነ

*** የሚኒስትሮችና ዳኞች ሹመቶች ፀደቁ

General Election 2013

Source: PD

የኢትዮጵያ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን  4ኛው አስቸኳይ ስብሰባው  6ኛው ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ እንዲካሄድ ወሰኗል። 

የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን በመከላከል ምርጫውን በ2013 ማካሄድ የሚቻልበትን የዓለም ጤና ድርጅትና የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክረ ሃሳቦች ተከትሎ ግብር ላይ እንዲውል ለምክር ቤቱ የውሳኔ ሃሳብና ሪፖርት ያቀረቡት የሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ አበባ ዮሴፍ  ናቸው፡፡

የውሰኔ ሃሳቡም የውሳኔ ሃሳብ ቁጥር 16/2013 ሰፍሮ በአንድ ተቃውሞ በ8 ድምጸ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምጽ ጸድቋል፡፡

በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች እንዲሁም በትምህርት ቤቶች ላይ ተጥለው የነበሩት የኮቨድ - 19 ወረርሽኝ ገደቦች ላልተው ክፍት እንዲሆኑ በምክር ቤቱ ውሳኔ ውስጥ ተካትቷል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ለምክር ቤት የቀረቡትን የሚኒስትሮችና ዳኞችን ሹመት ይሁንታ ቸሯል።

በዚህም መሰረት፦

  1. ዶ/ር ቀነዓ ያደታ የኢፌዴሪ የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር
  2. ዶ/ ጌዲዮን ጢሞቲዎስ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ
  3. ዶ/ር ሳሙኤል ሁርካቶ የኢፌዴሪ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር
  4. ኢንጅነር ታከለ ኡማ የኢፌደሪ ማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር ሚኒስትር በመሆን በምክር ቤቱ በ5 ድምጸ ተዓቅቦ ገጥሞት በአብላጫ ድምጽ ጸድቋል።
በተጨማሪም ምክር ቤቱ የ40 የከፍተኛ ፍርድ ቤት  እጩ ዳኞችን ሹመት በ5 ድምጸ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምፅ እንዲሁም የ50 የመጀመሪያ ፍርድ ቤት እጩ ዳኞችን ሹማት ደግሞ በ3 ድምጸ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል።

 


Share

Published

By Stringer Report

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service