ብልፅግና ፓርቲ ማኒፌስቶውን አስተዋወቀ

*** አዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደርን ጨምሮ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ጋምቤላ፣ ኦሮሚያ እና ሐረሪ ክልሎች የዕጩዎች ምዝገባ ዛሬ ይጀመራል

 Abiy Ahmed

Ethiopia's Prime Minister Abiy Ahmed. Source: Getty

 የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ብናልፍ አንዱዓለም እንዲሁም በመድረኩ የተገኙት የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝደንት ዐቢይ አሕመድ ፓርቲው በምርጫ ወቅት የሚጠቀምበትን ማኒፌስቶና የምርጫ መወዳደሪያ ምልክትን ይፋ አድርገዋል፡፡

“ሕብረ ብሔራዊ ወንድማማችነት ለጋራ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል የምርጫ 2013 የብልጽግና ፓርቲ ማኒፌስቶ እና የምርጫ መወዳደሪያ ምልክት ይፋዊ የእውቅና መድረክ በሸራተን አዲስ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

በመድረኩ በርካታ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

***

አዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደርን ጨምሮ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ጋምቤላ፣ ኦሮሚያ እና ሐረሪ ክልሎች የዕጩዎች ምዝገባ ዛሬ ይጀመራል

ምዝገባው የሚከናወነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለዕጩዎች ምዝገባ ባወጣው ከየካቲት 08 እስከ የካቲት 21 ቀን 2013 ዓ.ም የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ነው።

የምርጫ ክልሎቹ በተጠቀሱት ጊዜያት የዕጩዎች ምዝገባ የሚያከናውኑት ለምርጫ ክልል እና ለዞን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሊያገለግሉ የሚችሉ ቢሮዎችን በማዘጋጀታቸው መሆኑን ቦርዱ ገልጿል።

በአፋር፣  አማራ፣ ሲዳማ፣ ደቡብ  እና ሶማሌ ክልሎች ከየካቲት 05 እስከ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ለዕጩዎች ምዝገባ የሚውሉ ቁሳቁሶች እንደሚጓጓዙ እና የዕጩዎች ምዝገባ አስፈጻሚዎች ሥልጠና እንደሚሰጥም ቦርዱ አመልክቷል።

ከየካቲት 15 እስከ 26 ቀን 2013 ዓ.ም ደግሞ የዕጩዎች ምዝገባ እንደሚከናወን ቦርዱ ባለፈው ሳምንት መወሰኑ ይታወሳል።

[ደመቀ ከበደ ፡ አዲስ አበባ]


Share

Published

By Demeke Kebede

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service