የኢትዮጵያ አገር አቀፍ ምርጫ የድምፅ መስጫ ቀን ለግንቦት 28 ቀን ተቆረጠለት

*** የአዲስ አበባና የድሬደዋ ከተማ መስተዳድራት የድምጽ መስጫ ቀን ለሰኔ 5 ተይዟል፤ የጊዜ ሰሌዳው ትግራይን አያካትትም

Election 2021

Birtukan Mideksa, Chairperson of the National Election Board of Ethiopia . Source: Getty

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ድምጽ መስጫ ቀን ግንቦት 28 እንዲሆን በረቂቅ የጊዜ ሰሌዳው ላይ አሳውቋል።

የአዲስ አበባ ከተማ እና የድሬደዋ ከተማ መስተዳድር የድምጽ መስጫ ቀን ሰኔ 5 መሆኑን ገልጿል።

ቦርዱ ዝርዝር የጊዜ ሰሌዳውን ይፋ አድርጓል።

ይህ የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ የትግራይ ክልልን አያካትትም ተብሏል።
Election timetable
Ethiopia's general elections timetable Source: NEBE
የምርጫ ቢሮዎች መከፈት የክልል መስተዳድር አባላት ከፍተኛ ትብብር ስለሚያስፈልገው፤ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ይህንን ድጋፍ ለማድረግ ጊዜ ስለሚያስፈልገው እንዲሁም በክልሉ የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለምርጫ በሚስማማ መልኩ መመቻቸቱ ሲረጋገጥ በክልሉ የሚደረገው ምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ቦርዱ የሚያሳውቅ ይሆናል።

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ግንቦት 28 ቀን 2013 ዓ.ም የድምጽ መስጫ ቀን እንዲሆን ረቂቅ የጊዜ ሰሌዳ አቅርበው ዛሬ ውይይት  ተደርጎበታል።

የቀጣዩ  ሀገራዊ ምርጫን የጊዜ ሰሌዳ አስመልክቶ ቦርዱ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር  በአዲስ አበባ ራዲሰን ብሉ ሆቴል ተወያይቷል፡፡

በዚህ ስብሰባ በ2013 የሚደረገው ምርጫ አጠቃላይ የትግበራ መርሃ ግብር ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

 


Share

Published

Updated

By Demeke Kebede

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service