የኢትዮጵያ፣ ግብፅና ሱዳን ድርድር ዳግም ተራዘመ

*** "በድርድር የሚደረሰበት ስምምነት ብቸኛ አማራጭ በመሆኑ ኢትዮጵያ ለድርድሩ ውጤታማነት አበክራ ትሠራለች" - የኢትዮጵያ የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር

GERD talks

Source: Courtesy of PD

በሕዳሴ ግድብ ፕሮጄክት ላይ ትንናት ሰኞ ኦገስት 10 ሊካሄድ ተወጥኖ የነበረው የሶስትዮሽ ድርድር በሱዳን የይራዘምልኝ ጥያቄ ለመጪው ሳምንት ሰኞ ኦገስት 17 - 2020 ተሸጋግሯል።

ይህንኑ የድርድሩ ሂደት ለአንድ ሳምንት መስተጓጎልን የገለጠው የኢትዮጵያ የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ "አገራቱ [ግብፅና ሱዳን] ድርድሩን በመቀጠል የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ ቢሮ ስብሰባ በተካሄደ ሁለት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ የመካከለኛ እና የመጨረሻ ሪፖርት ለሕብረቱ ሊቀመንበር ሪፖርት እንዲያቀርቡ ይጠበቅ ነበር። ሆኖም ግብፅና ሱዳን ባቀረቡት ማራዘሚያ ምክንያት ባለፉት ባለፉት ሁለት ሳምንታት ድርድር ሳይካሄድ ቀርቷል" ብሏል።

አያይዞም፤ ጁላይ 24 - 2020 የአፍሪካ ሕብረት ጽሕፈት ቤት እንዲሁም ሐምሌ 27 - 2012 የሶስቱ ተደራዳሪ አገራት የውኃ ሚኒስትሮች በጋራ ታድመው የደረሱበትን መግባባት ተመርኩዞ ኢትዮጵያ "የግድብ ሙሌት ደንብ" ማቅረቧን አጣቅሷል።
ምንም እንኳ ቀጣዩ ታሳቢ ስብሰባ ስለመካሄዱ የተሰጠ ማስተማመኛ ባይኖርም በሚቀጥለው ሳምንት ሰኞ ነሐሴ 11 - 2012 (ኦገስት 17 - 2020) የሶስትዮሽ ድርድሩ ይቀጥል ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።

የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የስብሰባውን ፋይዳ አስመልክቶም "በድርድር የሚደረሰበት ስምምነት ብቸኛ አማራጭ በመሆኑ ኢትዮጵያ ለድርድሩ ውጤታማነት አበክራ ትሠራለች" ሲል ገልጧል።

የግብፅ የውኃና መስኖ ሚኒስቴር በበኩሉ "ግብፅ የሕዳሴ ግድብን ሙሌትና አጠቃቀም አስመልክቶ ሕጋዊ አስገዳጅነት ካለው ስምምነት ላይ ለመድረስ ዝግጁ ናት" ብሏል።

     

 

 



Share

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service