"በዚህ ወቅት ከዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የምንጠብቀው ትብብር ነው " የኢትዮጵያ መንግስት

*** "በትግራይ ክልል የተወሰነው የተናጠል የተኩስ አቁም በክልሉ ተጨማሪ ጥፋት እንዳይከሰት በማሰብ ነው" - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን

MOFA

State Minister Redwan Hussien (L) and Demeke Mekonnen, Deputy Prime Minister of Ethiopia and Minister of Foreign Affairs (R). Source: SBS Amharic/Demeke Kebede

ዛሬ ረፋድ የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ ወቅታዊ ጉዳይ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ላደረጉ የዲፕሎማሲ ማህበረሰብ አባላት በስካላይት ሆቴል ማብራሪያ እየሰጠ ነው።  ማብራሪያውን እየሰጡ የሚገኙት ምክትል ጠቅላይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንንና ምክትላቸው አቶ ሬድዋን ሁሴን ናቸው።

አቶ ደመቀ በንግግራቸው "በትግራይ ክልል የተወሰነው የተናጠል የተኩስ አቁም በክልሉ ተጨማሪ ጥፋት እንዳይከሰት በማሰብ ነው" ብለዋል።  አቶ ደመቀ አክለውም "በርካታ ሀብቶች የወደሙ በመሆኑ ከዚህ በላይ በሰው ሕይወትና በአገሪቱ ሃብት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለማስቀረት ነው።" ብለዋል።

ጉዳት የደረሰባቸውንና የወደሙ መሠረተ ልማቶችን መንግስታቸው መልሶ ሲገነባ እንደነበረ ያወሱት ምክትል ጠቅላይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በ " ሽብርተኛው ህወሓት" ተደጋጋሚ ጥቃት እየደረሰ ነው። ስለሆነም ከዚህ በላይ ሀብት ማባከንና ሕይወት መጥፋት ስለሌለበት ለክልሉ ዜጎች የጥሞና ጊዜ ተሰጥቷል ብለዋል።

"የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም ይህንን መረዳት ይገባዋል፤ በዚህ ወቅት ከዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የምንጠብቀውም ትብብር ነው" ያሉት አቶ ደመቀ መንግስታቸው በክልሉ ለሚገኙ ዜጎች አስፈላጊውን የሰብአዊ እርዳታ እንዲያገኙ ከአጋር አካላት ጋር እንደሚሰራም ተናግረዋል።

[ ደመቀ ከበደ ፡ አዲስ አበባ ]


Share

Published

By Demeke Kebede

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service