በትግራይ ክልል የሚቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር የሕዝቡን ራስን በራስ የማስተዳደር መብት የሚያስከብር እንደሚሆን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ አደም ፋራህ ገለጡ

*** የሚቋቋመው አስተዳደር የክልሉ ምክር ቤትና ካቢኔ ሲሰራቸው የነበሩ ተግባራትን እንደሚያከናውንም ተገልጿል።

Adam Farah

Adam Farah, Speaker of House of Federation Source: PD

የፌዴሬሽን ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲቋቋም በሙሉ ድምፅ ውሳኔ አሳልፏል። ውሳኔውን አስመልክቶም የምክር ቤቱ አፈጉባኤ አደም ፋራህ ለጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ “የሚቋቋመው አስተዳደር በሕገ መንግስቱ ድንጋጌዎች መሰረት የሚሰራና የትግራይን ሕዝብ ራስን በራስ የማስተዳደር መብት የሚያስከብር ይሆናል” ብለዋል።

 “ሕገወጡ የህወሓት ቡድን የትግራይ ሕዝብ ራስን በራስ የማስተዳደር መብት የሚከበረው በእሱ ብቻ እንደሆነ አድርጎ ሲንቀሳቀስ ቆይቷል” ብለዋል። ይህም የሕገ መንግስቱን መርሆዎች የሚፃረር እንደሆነ ነው የገለጹት።

ቡድኑ የፌዴሬሽንና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤቶች ውሳኔዎችን በመጣስ ኢ-ሕገ መንግስታዊ በሆነ መንገድ ሲንቀሳቀስ ቆይቶ በአገር መከላከያ ሠራዊት ላይ ጥቃት አድርሷል ሲሉም አስታውሰዋል።

በመሆኑም የፌዴሬሽን ምክር ቤት ቡድኑ ወደ ሕጋዊ መንገድ እንዲመጣ የተለያዩ ውሳኔዎችን ሲያሳልፍ የቆየ ቢሆንም ሊመጣ ባለመቻሉ የፌዴራል መንግስት ጣልቃ እንዲገባ፣ ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲቋቋምና የፌዴራል የፀጥታ አካል በክልሉ እንዲሰማራ ውሳኔ ማሳለፉን ተናግረዋል።

በትግራይ ክልል የሚቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር በአጭር ጊዜ የሚቋቋም ሲሆን ተጠሪነቱ ለፌዴራል መንግስት ይሆናል ተብሏል።

 የሚቋቋመው አስተዳደር የክልሉ ምክር ቤትና ካቢኔ ሲሰራቸው የነበሩ ተግባራትን እንደሚያከናውንም ተገልጿል።

 ኢዜአ እንደዘገበው ኃላፊነቱን ለመወጣትም እስከታችኛው መዋቅር ድረስ አስፈፃሚዎችን የሚመድብ ይሆናል ተብሏል።

 

 


Share

Published

By Stringer Report

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service