የገንዘብ ሚኒስቴር ለትግራይ ወረዳ ፣ ከተማና ቀበሌ የድጎማ በጀት የሚተላለፍበት የአሠራር ዝግጅት መጠናቀቁን አስታወቀ

*** በጀቱ በወረዳ፣ ከተማና ቀበሌ አስተዳደር አካላት የባንክ ሂሳብ በኩል ይተላለፋል

Ministry of Finance

Haji Ibssa Source: PD

የገንዘብ ሚኒስቴር ለትግራይ ወረዳ ፣ ከተማና ቀበሌ የድጎማ በጀት የሚተላለፍበት አሠራር ዝግጅት አጠናቅቄያለሁ አለ።

በሚኒስቴሩ የተዘጋጀው የበጀት ድጎማ አሠራር በሚቀጥለው ሣምንት ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቦ ከጸደቀ በኋላ ተግባራዊ ይደረጋል ብሏል።

በዚህም በጀቱ በወረዳ፣ ከተማና ቀበሌ አስተዳደር አካላት የባንክ ሂሳብ በኩል እንደሚተላለፍ ተገልጿል።

አስተዳደር አካላቱ የባንክ ሂሳብ ማስተላለፊያ ደብተር ካላቸው በዚያው በኩል ከሌላቸው ደግሞ አዲስ የባንክ ሂሳብ በመክፈት በጀቱ እንዲደርሳቸው ይደረጋል ነው የተባለው።

ሚኒስቴሩ የትግራይ ሕዝብ እንደ ሌሎቹ የአገሪቱ ክልል ሕዝቦች የትምህርት ፣ የጤና ፣ የንጹሕ መጠጥ ውኃ ፣ የምግብ ዋስትና እንዲሁም ሌሎች መሠረታዊ የሆኑ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ድጋፍ እንዲያገኙ ይደረጋል ብሏል።

የገንዘብ ሚኒስቴር የኮሙኒኬሽንና ኢንፎርሜሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሐጂ ኢብሳ እንዳሉት ከወረዳ ከተማና ቀበሌ የበጀት ድጋፍ አፈጻጸምን አስመልክቶ ለሚነሱ ጥያቄዎች የድጎማ በጀት የሚተላለፍበት አሠራር ዝርዝር በምክር ቤቱ ከጸደቀ በኋላ የሚገለጥ ይሆናል። 

[ኢዜአ ]


Share

Published

By Stringer

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
የገንዘብ ሚኒስቴር ለትግራይ ወረዳ ፣ ከተማና ቀበሌ የድጎማ በጀት የሚተላለፍበት የአሠራር ዝግጅት መጠናቀቁን አስታወቀ | SBS Amharic