በዓመታዊው የአምባሳደሮች ሴሚናር የተሻሻለው የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ረቂቅ ሰነድ ሊመከርበት ነው

*** ኮቪድ 19 በዲፕሎማሲ ሥራ ላይ ጫና አሳድሯል

MOFA Press Conference

Ambassador Dina Mufti, Ethiopian Foreign Ministry Spokesperson Source: Courtesy of DK

የኢትዮጵያ አምባሳደሮች እና ዲፕሎማቶች በተሻሻለው የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ረቂቅ ሰነድ ላይ ከሰኞ ጀምሮ ይወያያሉ።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳሉት ውይይቱ ከመጪው ሰኞ ነሐሴ 18 ቀን 2012 ጀምሮ  ለሁለት ሳምንታት በቢሾፍቱ ይካሔዳል።

በዚህ በዓመታዊው  የአምባሳደሮች ሴሚናር ላይ  ረቂቅ ፖሊሲው የበለጠ ትኩረት የሚያገኝ ይሁን እንጂ የኤምባሲዎችና ቆንስላዎች የሥራ አፈፃፀም ይገመገማል።

የወደፊት የስራ መመሪያዎችም እንደሚተላልፉ ተገልጧል።

አምባሳደር ዲና፤ በኮቪድ 19 የተነሳ አጠቃላይ የዲፕሎማሲ ሥራው ጫና ውስጥ መግባቱንና በዚህ የተነሳም እንደሚፈለገው እየተሠራ እንዳልሆነ አክለው ገልፀዋል።

በተለይ የቱሪዝም ሴክተሩ መዳከሙንና በዓረብ አገራት በችግር ላይ ያሉ ዜጎችን ለመታደግ ወቅቱ አስቸጋሪ መሆኑን ጠቅሰዋል።

አብዛኞቹ ዜጎች በኢሚግሬሽን በኩል ያላለፉ፣ ህጋዊ ዶክመንት የሌላቸው በመሆናቸውና በውጭ አገራት ባሉን ኤምባሲዎችም ምዝገባ ስለማያደርጉ ለማገዝና ለመርዳት አስቸጋሪ ሆኗል ብለዋል ቃል አቀባዩ።

በዚህ አስቸጋሪ የኮቪድ 19 ሁኔታ ውስጥ ብንሆንም በየአገራቱ ያሉ ኤምባሲዎችና ቆንስላዎች የዜጎችን ጉዳይ በትኩረት እንዲከታተሉ ጥብቅ መመሪያ በውጭ ጉዳይ በኩል ተሰጥቷል። እንደ አውሮፓ ህብረት ካሉ ተቋማት ጋርም እየሰራን ነው ሲሉ አክለዋል።

 ቃል አቀባዩ ሌላው ያነሱት የህዳሴ ግድቡ ድርድር ጉዳይ ሲሆን አሁንም እንደቀጠለ ነው ብለዋል።

 " በኢትዮጵያ በኩል በትጋት እየተደራደርን ነው። ድርድሩ ሂደት ላይ ነው አሁንም ፣  ውጤት ሲኖር በይፋ እናሳውቃለን" ብለዋል።

 


Share

Published

By Demeke Kebede

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
በዓመታዊው የአምባሳደሮች ሴሚናር የተሻሻለው የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ረቂቅ ሰነድ ሊመከርበት ነው | SBS Amharic