የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገዱ አንዳርጋቸው በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደርን ጠርተው ፕሬዚዳንት ትራምፕ በሕዳሴ ግድብ ላይ በሰጡት አስተያየት ላይ ማብራሪያ ጠየቁ

*** የፕሬዚደንቱን ንግግር ከጦር ጫሪነት ጋር አያይዘውታል

MOFAE GERD

Mike Raynor, US Ambassador to Ethiopia (L), and Gedu Andargachew, Minister of Foreign Affairs of Ethiopia (R) Source: MOFAE

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገዱ አንዳርጋቸው በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ማይክ ሬይኖርን በጽህፈት ቤታቸው ጠርተው ማብራሪያ ጠየቁ።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አምባሳደር ማይክ ሬይኖርን ትናንት በጽህፈት ቤታቸው አስጠርተው ፕሬዚዳንት ትራምፕ በሕዳሴ ግድብ ላይ በሰጡት አወዛጋቢ አስተያየት ዙሪያ  ማብራሪያ ጠይቀዋል።

ትራምፕ አወዛጋቢውን አስተያየት የሰጡት ከሱዳን እና ከእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትሮች ጋር የስልክ  ውይይት ባደረጉበት ወቅት ነው፡፡

አቶ ገዱ በዚህ ወቅት የታላቁ ሕዳሴ ግድብን የዓባይን የውኃ ፍሰት እንደማይገታ ሁሉ ሕዳሴ ግድብንና የድርድሩን ሂደት አስመልክቶ የተሰጠው መግለጫ አሳሳችና ስሕተትንም የተላበሰ መሆኑን አበክረው አስታውቀዋል።

አክለውም፤ በኢትዮጵያና በግብፅ መካከል ጦርነት ቀስቃሽነት በስልጣን ላይ ካለ ፕሬዚደንት የማይጠበቅ እንዲሁም በኢትዮጵያና በአሜሪካ መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ አጋርነትና ስትራቴጂካዊ ግንኙነትን የማያንፀባርቅና ዓለም አቀፍ ሕግ በሚገዛቸው አገራት ግንኙነት ዘንድ ተቀባይነት ያለው አለመሆኑንም ገልጠዋል።

ሚኒስትሩ - ኢትዮጵያ ከቶውንም ባለፉትም ሆነ ለወደፊቱ በሉዓላዊነቷ ላይ በሚሰነዘሩ ማናቸውም ዛቻዎች የማትንበረከክና የሶስትዮሹንም ድርድር በአፍሪካ ሕብረት ማዕቀፍ ለመቀጠል የማታወላዳ መሆኑን ለአምባሳደሩ አስታውቀዋል።


Share

Published

Updated

By Stringer Report

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገዱ አንዳርጋቸው በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደርን ጠርተው ፕሬዚዳንት ትራምፕ በሕዳሴ ግድብ ላይ በሰጡት አስተያየት ላይ ማብራሪያ ጠየቁ | SBS Amharic