የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገዱ አንዳርጋቸው በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደርን ጠርተው ፕሬዚዳንት ትራምፕ በሕዳሴ ግድብ ላይ በሰጡት አስተያየት ላይ ማብራሪያ ጠየቁ

*** የፕሬዚደንቱን ንግግር ከጦር ጫሪነት ጋር አያይዘውታል

MOFAE GERD

Mike Raynor, US Ambassador to Ethiopia (L), and Gedu Andargachew, Minister of Foreign Affairs of Ethiopia (R) Source: MOFAE

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገዱ አንዳርጋቸው በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ማይክ ሬይኖርን በጽህፈት ቤታቸው ጠርተው ማብራሪያ ጠየቁ።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አምባሳደር ማይክ ሬይኖርን ትናንት በጽህፈት ቤታቸው አስጠርተው ፕሬዚዳንት ትራምፕ በሕዳሴ ግድብ ላይ በሰጡት አወዛጋቢ አስተያየት ዙሪያ  ማብራሪያ ጠይቀዋል።

ትራምፕ አወዛጋቢውን አስተያየት የሰጡት ከሱዳን እና ከእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትሮች ጋር የስልክ  ውይይት ባደረጉበት ወቅት ነው፡፡

አቶ ገዱ በዚህ ወቅት የታላቁ ሕዳሴ ግድብን የዓባይን የውኃ ፍሰት እንደማይገታ ሁሉ ሕዳሴ ግድብንና የድርድሩን ሂደት አስመልክቶ የተሰጠው መግለጫ አሳሳችና ስሕተትንም የተላበሰ መሆኑን አበክረው አስታውቀዋል።

አክለውም፤ በኢትዮጵያና በግብፅ መካከል ጦርነት ቀስቃሽነት በስልጣን ላይ ካለ ፕሬዚደንት የማይጠበቅ እንዲሁም በኢትዮጵያና በአሜሪካ መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ አጋርነትና ስትራቴጂካዊ ግንኙነትን የማያንፀባርቅና ዓለም አቀፍ ሕግ በሚገዛቸው አገራት ግንኙነት ዘንድ ተቀባይነት ያለው አለመሆኑንም ገልጠዋል።

ሚኒስትሩ - ኢትዮጵያ ከቶውንም ባለፉትም ሆነ ለወደፊቱ በሉዓላዊነቷ ላይ በሚሰነዘሩ ማናቸውም ዛቻዎች የማትንበረከክና የሶስትዮሹንም ድርድር በአፍሪካ ሕብረት ማዕቀፍ ለመቀጠል የማታወላዳ መሆኑን ለአምባሳደሩ አስታውቀዋል።


1 min read

Published

Updated

By Stringer Report


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now