ሐሙስ ምርጫ በሚከናወንባቸው አካባቢዎች ሥራ ዝግ እንደሚሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ

*** መስከረም 20/2014 ዓም 6ኛው አጠቃላይ ምርጫ ባልተከናወነባቸው ቀሪ የምርጫ ክልሎች እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝበ ውሳኔ እንደሚደረግ ቦርዱ አስታውቋል።

Solyana Shimelis, spokeswoman of the National Electoral Board of Ethiopia.

Solyana Shimelis, spokeswoman of the National Electoral Board of Ethiopia. Source: SBS Amharic

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ኮሙኒኬሽን ኃላፊ ወ/ሪት ሶሊያና ሽመልስ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳሉት በሐረሪ ክልል፣ በሶማሊ ክልል፣ በደቡብ ክልል ምዕራብ ኦሞ ዞን፣ በደቡብ ኦሞ ዞን፣ በቤንች ሸኮ ዞን፣ በሸካ ዞን፣ በጌዲዮ ዞን፣ በሃድያ ዞን፣ በጉራጌ ዞን ፣ በጋሞ ዞን፣ በካፋ ዞን፣ በወላይታ ዞን፣ በዳውሮ ዞን፣ በባስኬቶ ልዩ ወረዳ እና በኮንታ ልዩ ወረዳ ምርጫውን ዜጎች ማከናወን እንዲችሉ ሥራ ዝግ እንደሚሆን አስታውቀዋል።

ምርጫው ከጠዋቱ 12:00 እስከ ምሽት 12:00 ይከናወናል ያሉት ሶልያና በ የምርጫ ክልሎች ቁሳቁሶች መድረሳቸውንና በቀሩ ጥቂት ጣቢያዎችም ከምርጫ ሰዓት በፊት ተደራሽ ይደረጋል ብለዋል።

ለነገው ምርጫ መሰረታዊ የሆነ የፀጥታም ይሁን የቁሳቁስ ችግር እስካሁን አላጋጠምም ብለዋል ሶሊያና።

ምርጫውን 11 አገር በቀል ተቋማት 1690 ታዛቢዎቻቸውን የሚያሰማሩ ሲሆን ከእነዚህ አምስቱ በሁሉም አካባቢዎች የሚታዘቡ ሲሆን ቀሪዎቹ በየሚሰሩባቸው አካባቢዎች ይታዘባሉ።

ሐሙስ ዕለት ምርጫ ከሚደረግባቸው አካባቢዎች ውጪ ባሉት የአገሪቱ ክፍሎች ሰኔ 14/2013 ዓም አጠቃላይ ምርጫ መካሄዱና መንግስት መመስረት የሚያስችለውን አብዛኛውን ድምፅ ብልፅግና ፓርቲ ማሸነፉ ይታወሳል።

[ ደመቀ ከበደ ፡ አዲስ አበባ ]


1 min read

Published

By Demeke Kebede


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now