የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ6ተኛው አገራዊ ምርጫ የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶች ግዢ ከ90 በመቶ በላይ እንደተጠናቀቀ አስታወቀ

*** በአገር አቀፉ ምርጫ የ50,000,000 መራጮች ድምፅ ይጠበቃል

NEBE

Board members Source: SBS Amharic

ቦርዱ ለአገራዊ ምርጫ ኦፕሬሽን እያደረገ ያለውን ዝግጅት እና በተለያዩ መጋዘኖቹ ገዝቶ ያከማቻቸውን የተለያዩ የምርጫ ቁሳቁሶችን በኤግዚቪሽን ማዕከልና በቦሌ ጉምሩክ መጋዘኖቹ ለጋዜጠኞች እያስጎበኘ ነው።

ቦርዱ ከዚህ ቀደም ከተካሄዱ ምርጫዎች በተለየ ምርጫን በአስተማማኝ ሁኔታ ለማካሄድ የሚያስችል የምርጫ ቁሳቁሶች ግዢ ማድረጉን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።

ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ ሲተገበር የነበረው የምርጫ ሂደት እና ቀጣይ ሊደረግ የታቀደው የምርጫ ሂደት ቁሳቁስ ልዩነት ምን እንደሚመስል በማነፃፀርም የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲያዩ እየተደረገ ነው።
National Elections
Source: NEBE
የአገር አቀፍ ምርጫ ኦፕሬሽን ዝግጅቶች

  • የምርጫ ጣቢያ ብዛት - 50,900
  • የሚጠበቁ መራጮች ቁጥር - 50,000,000
የአስፈጻሚዎች ቁጥር

  • ለመራጮች ምዝገባ - 152,700
  • ለድምፅ መስጫ ቀን - 254,500
ለመራጮች ምዝገባ የተዘጋጁ ቁሳቁሶች

  • በአምስት ቋንቋዎች የተዘጋጁ የመራጮች መዝገቦች - 50,900 ጥራዞች
ለስልጠና የሚውሉ ሕትመቶች (በአምስት ቋንቋዎች የተዘጋጁ) - 8,200

የድምፅ መስጫ ቀን ቁሳቁሶች

  • በግልጽ የሚያሳዩ የድምፅ መስጫ ሳጥኖች (በአንድ ጣቢያ አራት የድምፅ መስጫ ሳጥን ድረስ) - 207,000
  • የምስጢር ድምፅ መስጫ መከለያዎች - 156,600
  • ማስፈጸሚያ ቁሳቁስ የያዙ ሰማያዊ ሳጥን - 50,900
  • መከፈታቸውን የሚያሳውቁ ቦርሳዎች - 712,600
  • የጠረጴዛ ባትሪዎች - 110,800
 መጪው አገር አቀፍ ምርጫ ኮቪድ -19ን ታሳቢ ያደረገ እንዲሆን የጥንቃቄ ቁሳቁሶችን እንደሚያሟላ ቦርዱ አስታውቋል።


Share

Published

Updated

By Demeke Kebede

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service