ምርጫ ቦርድ በምርጫ ሂደት የኮሮናቫይረስ ለመከላከል ያወጣውን መመሪያ ለሕዝብ አስተያየት ክፍት አደረገ

*** የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

NEBE: CVID - 19

Birtukan Mideksa, Chairperson of the National Election Board of Ethiopia. Source: Getty

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቀጣዩን ስድስተኛ ሀገራዊ ምርጫ ለማካሄድ የተለያዩ መመሪያዎችን እያፀደቀ ነው፡፡ ከእነዚህ የምርጫ መመሪያዎች አንዱ የሆነውን በምርጫ ሂደት ወቅት የኮሮናቫይረስን ለመከላከል የሚያስችል ረቂቅ መመሪያ አውጥቶ ለአንድ ሳምንት የሚቆይ የሕዝብ አስተያየት ክፍት ማድረጉን አስታውቋል፡፡

የረቂቅ መመሪያው ዋና ዓላማ በቅድመ ምርጫ፣ በድምፅ መስጫ ቀን እና በድህረ ምርጫ ወቅት ከምርጫ ጋር ተያያዥ ተግባራት ሁሉ የቫይረሱን ስርጭት እንዳይጨምር ማድረግ ነው ተብሏል፡፡

ረቂቅ መመሪያው ለቦርዱ፣ ለምርጫ ባለድርሻ አካላት እና አስፈፃሚዎች ኮሮናቫይረስን ለመከላከል ያስፈልጋሉ በሚባሉ ጉዳዮች ዙሪያ ትኩረት ያደረገ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡

ረቂቅ መመሪያውን ከሕዝብ በሚሰበሰብ ገንቢ አስተያየት ለማዳበር ይረዳ ዘንድ ለአንድ ሳምንት ለሚቆይ ጊዜ ክፍት ተደርጓል፡፡ ረቂቅ መመሪያው ከዛሬ ጀምሮ ለሕዝብ አስተያየት ክፍት መሆኑን የገለፀው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በረቂቁ ዙሪያ ለሚኖር ሀሳብና አስተያየት በኢሜል አድራሻ legal@nebe.org እንዲሁም በቦርዱ ገጽ መልዕክት ማስቀመጫ አማካኝነት መላክ እንደሚቻል አስታውቋል፡፡

ለተጨማሪ መረጃ:- ረቂቅ መመሪያውን ለማግኘት ተከታዩን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም መጫን ይቻላል፡፡ https://urldefense.com/v3/__https://bit.ly/3ofdkAn__;!!MiK4Rck!B0A1vsGswyI26UFseFez3HrowKqD5CAFzUp9uROxExjWHX6_BSoMyFd6QycbgzwVZhPA$

[ምርጫ ቦርድ]


Share

Published

By Stringer Report

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service