የፓርቲዎች የምርጫ ምልክት ይፋ ሆነ

*** "በሕጋዊነት የተመዘገቡ ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወስደዋል" - የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

NEBE

Birtukan Mideksa, Chairperson of the National Election Board of Ethiopia. Source: Getty

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እንዳስታወቀው "በህጋዊነት የተመዘገቡ ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወስደዋል" ብሏል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ተኛው አገር አቀፍ ምርጫን ለማከናወን በጊዜ ሰሌዳው ላይ ካስቀመጣቸው ተግባራት መካከል አንደኛው የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ምልክቶቻቸውን የሚመርጡበት/ የሚያስገቡበት መርሃ ግብር ነው። 

በዚሁ የጊዜ ሰሌዳ መሰረትም ከጥር 13 ቀን እስከ ጥር 24 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ ፓርቲዎች ምልክት የሚያስገቡበት እና ቦርዱ አጣርቶ እንደሚያፀድቅ ተገልጿል።

ቦርዱ ይፋ እንዳደረገው በህጋዊነት የተመዘገቡ ሲል የገለፃቸው ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን መርጠው ያስገቡ ሲሆን ብሔራዊ ምርጫ ቦርድም ዛሬ ማፅደቁን ገልጿል።

በዚህም መሰረት ምልክቶቻቸው በቦርዱ የፀደቀላቸው 49 የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ይፋ ሆነዋል። 

[ ደመቀ ከበደ ፡ አዲስ አበባ ]


1 min read

Published

Updated

By Demeke Kebede



Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now