የ6ኛው አገር አቀፍ የመጨረሻ የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ይፋ ተደረገ

*** የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

NEBE

Birtukan Mideksa, Chairperson of the National Election Board of Ethiopia. Source: NEBE

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛውን አገር አቀፍ የመጨረሻ የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ዛሬ ይፋ አድርጓል።

ከዚህ ቀደም ታኅሣሥ 16 ቀን 2013 ዓ.ም የቦርዱ አመራሮችና ፖለቲካ ፓርቲዎች በተገኙበት የመጪው አገር አቀፍ ምርጫን ጊዜያዊ የጊዜ ሰሌዳ ለውይይት አቅርቦ ነበር።

በወቅቱ በውይይቱ ላይ የተሳተፉት የፖለቲካ ፓርቲዎች ጥያቄዎችንና አስተያየቶችን አቅርበው፣ ቦርዱ እጩዎችን ለማቅረብ የሚያስፈልገውን ፊርማ የሕግ መስፈርት ለ6ኛው አገራዊ ምርጫ ብቻ አገልግሎት ላይ እንዳይውል የተወካዮች ምክር ቤትን ጠይቆ እንደነበር ይታወሳል።

ምርጫ ቦርድ ትናንት አመሻሽ ላይ የመጨረሻው ያለውን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል።
NEBE
Source: NEBE
ቦርዱ ለ ኤስ ቢ ኤስ በላከው የኢሜል መግለጫ እንዳረጋገጠው የተግባራቱን አፈጻጸም ሰሌዳ ይፋ ያደረገ ሲሆን ወደፊትም ያሉበትን ሁኔታ እንደሚያሳውቅ አስታውቋል።

የመጨረሻ ባለው የጊዜ ሰሌዳ ባለፈው በምክክሩ ወቅት ከገለፀው የተለየ ማሻሻያ ያላደረገ ሲሆን ምርጫው ግንቦት 28/2013 ዓም የሚካሄድ ይሆናል።

[ደመቀ ከበደ ፡ አዲስ አበባ]


Share

Published

Updated

By Demeke Kebede

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service