የ6ኛው አገር አቀፍ የመጨረሻ የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ይፋ ተደረገ

*** የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

NEBE

Birtukan Mideksa, Chairperson of the National Election Board of Ethiopia. Source: NEBE

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛውን አገር አቀፍ የመጨረሻ የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ዛሬ ይፋ አድርጓል።

ከዚህ ቀደም ታኅሣሥ 16 ቀን 2013 ዓ.ም የቦርዱ አመራሮችና ፖለቲካ ፓርቲዎች በተገኙበት የመጪው አገር አቀፍ ምርጫን ጊዜያዊ የጊዜ ሰሌዳ ለውይይት አቅርቦ ነበር።

በወቅቱ በውይይቱ ላይ የተሳተፉት የፖለቲካ ፓርቲዎች ጥያቄዎችንና አስተያየቶችን አቅርበው፣ ቦርዱ እጩዎችን ለማቅረብ የሚያስፈልገውን ፊርማ የሕግ መስፈርት ለ6ኛው አገራዊ ምርጫ ብቻ አገልግሎት ላይ እንዳይውል የተወካዮች ምክር ቤትን ጠይቆ እንደነበር ይታወሳል።

ምርጫ ቦርድ ትናንት አመሻሽ ላይ የመጨረሻው ያለውን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል።

NEBE
Source: NEBE

ቦርዱ ለ ኤስ ቢ ኤስ በላከው የኢሜል መግለጫ እንዳረጋገጠው የተግባራቱን አፈጻጸም ሰሌዳ ይፋ ያደረገ ሲሆን ወደፊትም ያሉበትን ሁኔታ እንደሚያሳውቅ አስታውቋል።

የመጨረሻ ባለው የጊዜ ሰሌዳ ባለፈው በምክክሩ ወቅት ከገለፀው የተለየ ማሻሻያ ያላደረገ ሲሆን ምርጫው ግንቦት 28/2013 ዓም የሚካሄድ ይሆናል።

[ደመቀ ከበደ ፡ አዲስ አበባ]


1 min read

Published

Updated

By Demeke Kebede


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now