አምስት ፓርቲዎች የምርጫ ምልክቶቻቸውን እንዲቀይሩ ምርጫ ቦርድ አሳሰበ

*** እስከአሁን 45 ያህል የፖለቲካ ፓርቲዎች ምልክቶቻቸውን አስገብተዋል

NEBE

Birtukan Mideksa, Chairperson of the National Election Board of Ethiopia. Source: Getty

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የፓርቲዎች የምርጫ ምልክት መረጣ እየተከናወነ ይገኛል።

እስከአሁን ድረስ 45 ያህል ፓርቲዎች ምልክቶቻቸውን ማስገባታቸውን ታውቋል።

የሚከተሉት ፓርቲዎች የመረጧቸው ምልክቶች በተለያዩ ምክንያቶች ቀይረው እንዲያቀርቡ ጥሪ እንደተደረገላቸው ቦርዱ አሳውቋል ፦

1ኛ. የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ - የመረጠው ምልክት ከዚህ በፊት በነበረው ምርጫ ሌላ ፓርቲ ሲጠቀምበት የነበረ በመሆኑ እና ፓርቲው የቀድሞ ምልክቱን ለመጠቀም በመጠየቁ

2ኛ. የጋሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ- የመረጠው ምልክት ከዚህ በፊት በነበረው ምርጫ ሌላ ፓርቲ ሲጠቀምበት የነበረ በመሆኑ እና ፓርቲው የቀድሞ ምልክቱን ለመጠቀም በመጠየቁ

3ኛ. የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) - የመረጠው ምልክት ከዚህ በፊት በነበረው ምርጫ ሌላ ፓርቲ ሲጠቀምበት የነበረ በመሆኑ እና ፓርቲው የቀድሞ ምልክቱን ለመጠቀም በመጠየቁ

4ኛ. የምዕራብ ሶማሌ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ - ከሌላ ፓርቲ ምልክት ጋር ምልክቱ የተቀራረበ በሆኑ

5ኛ. የአርጎባ ብሔረሰብ ዴሞክራሲያቂ ንቅናቄ- ከሌላ ፓርቲ ምልክት ጋር ምልክቱ የተቀራረበ በመሆኑ

 6ኛ. የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) - ህጋዊ ሃላፊነት በተሰጠው አካል ምልክታቸውን እንዲመርጡ የተጠየቁ (በዚህም መሰረት የድርጅቱ ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ የምርጫ ምልክት አስገብተዋል።) 

የምርጫ ምልክት ያላስገቡ፣ እንዲቀይሩ የተገለፀላቸው ወይም መቀየር የሚፈልጉ እስከ ጥር 23 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ እንዲያጠናቁ ቦርዱ አሳስቧል።

የጸደቁ ምልክቶችን እና የፓርቲዎች ዝርዝር ሂደቱ ሲጠናቀቅ ይፋ የሚያደርግ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ገልጿል።

 


Share

Published

By Stringer Report

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service