አቶ ለማ መገርሳ ከብልፅግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ታገዱ

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳጋቶ ኮምቤ በመከላከያ ሠራዊት በቁጥጥር ስር ዋሉ

Prosperity Party

Lemma Megersa (L) and Dagato Kumbe (R) Source: Courtesy of PD

የኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲ ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን ስብሰባ ሲያጠናቅቅ በወሰዳቸው የፓርቲ ዲሲፕሊን እርምጃዎች ሶስት ከፍተኛ የአመራራ አባላቱን ከማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት አግዷል። 

ፓርቲው ያገዳቸው የአመራራ አባላት አቶ ለማ መገርሳ፣ ዶ/ር ሚልኪሳ ሚደጋና ወ/ሮ ጠይባ ሃሰን ናቸው።

የአገር መከላከያ ሚኒስትር ስልጣን ላይ ተቀምጠው ያሉት አቶ ለማ መገርሳ ከብልፅግና ፓርቲ የእግድ እርምጃ ሊወሰድባቸው የቻለው የፓርቲ ዲሲፕሊን ባለመጠበቅ፣ የአቋምና የአመላከካት ልዩነቶችን በፓርቲ መድረክ ውጪ ማንጸባረቅ፣ ልዩነቶችን ለመፍታት ጥረቶች ተደርገው ከስምምነት ላይ ቢደረስም በፓርቲው መድረክም ሆነ በመደበኛ የሥራ ገበታቸው ላይ ባለመገኘታቸው እንደሆነ ፓርቲው በማጠቃለያ መግለጫው አስታውቋል።

ሁለተኛው ታጋጅ ዶ/ር ሚልኬሳ ሚዳጋም በተመሳስይ መልኩ የአተያይና የአቋም ልዩነቶችን ለፓርቲው ከማቅረብ ይልቅ ከፓርቲው ዲሲፕሊን ውጪ የሆኑ አማራጮችን እንደተጠቀሙና የፓርቲውን ምስጢር ለሌሎች ሃይሎች አሳልፎ በመስጠት የዲሲፕሊን እርምጃ እንደተወሰደባቸው ተገልጧል።

ወ/ሮ ጠይባ ሃሰን በበኩላቸው በቅርቡ በምዕራብ አርሲ ተከስቶ ከነበረው የሰላም መደፍረስ ጋር በተያያዙ ጉዳዮች፣ የፓርቲውን ምስጢር ለሌሎች በማቀበል፣ በፓርቲው መድረኮችም ሆነ በመደበኛ ሥራቸው ላይ ባለመገኘታቸው የእገዳ ዲስፒሊናዊ እርምጃ እደተወሰደባቸው ተነግሯል።

ይኼው በኮንፈረሱ የተላለፈው የእገዳ እርምጃ  ለፓርቲው የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ቀርቦ ይሁንታን እንደሚያገኝ ይጠበቃል።

ውሳኔው በሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ከጸደቀ ከፓርቲ ዲሲፕሊናዊ እርምጃ ባሻገርም የሕጋዊ እርምጃ ምልከታዎችም እንደሚከተሉ ተጠቁሟል።  

የኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲ  በወቅታዊ አገራዊና ክፍለ አገራዊ ጉዳዮች ላይ መምከሩንም የኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ ገልጠዋል።

አክለውም፤ ኮንፈረንሱ 'ሕወሓትና ኦነግ ሸኔ ከውጭ ሀይሎች ጋር በመተባበር የታላቁን የኢትዮጵይ ህዳሴ ግድብ ግንባታን እና በሀገሪቱ እየተካሄደ ያለውን ለውጥ ለማደናቀፍ ከውጭ ከውጭ ሀይሎች ጋር ተባብረው እየሰሩ መሆኑን ተመልክቷል' ሲሉ ተናግረዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳጋቶ ኮምቤን ጨምሮ የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች ትናንት በመከላከያ ሠራዊት አባላት መያዛቸው ተገልጿል።

አልአይን እንደዘገበው አመራሮቹ ስብሰባ ላይ በነበሩበት ወቅት የተያዙ ሲሆን ከዚሁ ጋር በተያያዘ በከተማው  ሁከት መከሰቱም ገልጿል።

 የዞኑ አመራሮች ከክልል ጥያቄ ጋር በተያያዘ ከፌዴራልና ከደቡብ ክልል መንግሥት ጋር ቅራኔ ውስጥ መግባታቸው ይታወቃል። 

የዞኑ ክልል የመሆን ጥያቄ በደቡብ ክልል መንግሥት ተገቢው ምላሽ አልተሰጠውም በሚል ተቃውሞ በክልሉ ምክር ቤት የዞኑ ተወካዮች ራሳቸውን ከምክር ቤት አባልነት ካገለሉ ከስድስት ሳምንታት በላይ ተቆጥረዋል።



Share

Published

By Stringer Report

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service