ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ የአውስትራሊያ "አንድ ቻይና" ፖሊሲ አቋም ያልተቀየረ መሆኑን አስታወቁ

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይሁንታ የተቸረው ረቂቅ የአየር ንብረት ለውጥ ድንጋጌ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ፅድቅን እየጠበቀ ነው

 PM Anthony Albanese .jpg

Prime Minister Anthony Albanese speaks at the Sydney Energy Forum on July 12, 2022 in Sydney, Australia. . Source: Getty / Brook Mitchell

ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ አውስትራሊያ ታይዋንን አስመልክቶ ያላት አቋም ያልተቀየረ መሆኑንና በ"አንድ ቻይና" ፖሊሲ ፀንታ ያለች መሆኑን አስታወቁ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአውስትራሊያን አቋም ዳግም ግልፅ ለማድረግ ግድ የተሰኙት ቻይናን ካስቆጣው የዩናይትድ ስቴትስ አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት ጋር ተያይዞ ነው።

ከአፈ ጉባኤ ፔሎሲ ጉዞ ጋር ተያይዞ ቻይና በታይዋን ዙሪያ ወታደራዊ ሮኬቶችን መወንጨፏ ለአካባቢው አገራት አሳሳቢ ሆኗል። ፍኖም ፔን ካምቦዲያ በሚካሔደው የደቡብ ምሥራቅ እስያ አገራት ማኅበር 47ኛው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትራት ጉባኤ ታዳሚዋ የአውስትራሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፔኒ ዎንግ ውጥረቶችን እንዲረግቡ ጥሪ አቅርበዋል።

***

የአውስትራሊያ ፌዴራል መንግሥት የአየር ለውጥ ረቂቅ ድንጋጌው በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አብላጫ ድጋፍ አግኝቶ ማለፉን ተከትሎ "የአሠርት ዓመት ውዥቀት" አክትሟል ሲል ገለጠ።

ረቂቅ ድንጋጌው ፀድቆ በሕግነት ግብር ላይ ለመዋል የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ይሁንታን ማግኘት ግድ ይለዋል። ሆኖም 12 የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ያለው ግሪንስ ፓርቲ ለድንጋጌው መፅደቅ ድጋፉን እንደሚቸር በይፋ አስታውቋል።  

ረቂቅ ድንጋጌው ለሕግነት ለመብቃት 12 የግሪንስ ፓርቲንና አንድ የግል የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት አባልን ድምፅ ይሻል።

 ለረቂቅ ድንጋጌው ድጋፉን የነፈገው የተቃዋሚ ቡድን መሪ ፒተር ዳተን የመንግሥት 43 ፐርሰንት የአየር ብክለት ቅነሳ ዒላማ የኃይል ዋጋ ጭማሪን ሊያስከትል እንደሚችል አመላክተዋል።

ሆኖም የታዝማኒያ ሊብራል ፓርቲ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት ብሪጅት አርቸር ከፓርቲያቸው የተቃውሞ አቋም ተነጥለው ድምፃቸውን ለሌበር መንግሥት ሰጥተዋል።



 



Share

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ የአውስትራሊያ "አንድ ቻይና" ፖሊሲ አቋም ያልተቀየረ መሆኑን አስታወቁ | SBS Amharic