ልዑል ኤርሚያስ ሳህለሥላሴ በዓለም ትልቁ ጦርነት ዩክሬይንና መካከለኛው ምሥራቅ ሳይሆን ኢትዮጵያ እንደሆነ አመላከቱ

ልዑል ኤርሚያስ ሳህለ ሥላሴ ኃይለ ሥላሴ፤ የኢትዮጵያ ዘውድ ምክር ቤት ፕሬዚደንት በተገኙበት 82ኛው የጎንደር ድል ክብረ በዓል በለንደን ተከብሯል።

Victory of Gondar Dinner.jpg

Victory of Gondar Dinner. Credit: CCE

የዘውድ ምክር ቤት ፕሬዚደንቱ ኢትዮጵያውያንና የእንግሊዝ የክብር እንግዶች በተገኙበት ሕዳር 7 በተዘከረው የጎንደር ድል የእራት ግብዣ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ በአሁኑ ወቅት በዓለም ላይ ሕልፈተ ሕይወትና መፈናቀልን አስመልክቶ ትልቁ ጦርነት ኢትዮጵያ ውስጥ መሆኑን አመላክተዋል።

ይህንኑ ሲገልጡም፤

"ባለፉት ዓመታት 1.5 ሚሊየን ያህል ሰዎች ተገድለዋል፤ 26 ሚሊየን ያህል ከቤታቸው ተፈናቅለዋል። በዩክሬይንና እሥራኤል ሕልፈተ ሕይወትና ትርጉመ ሕይወት ሁኔታዎች ዓለምን በሐዘኔታ እንቀላቀላለን፤ ስለምን የመከራን ምንንነት እናውቃለንና" ብለዋል።

በዘንድሮው የጎንደር ድል በዓል በአገረ እንግሊዝ ንጉሥ ቻርልስ ሳልሳዊ ሞገስ አላባሽነት ለጎንደር ድል በክብር ለወደቁት የእንግሊዝና ኢትዮጵያ አርበኞች መዘከሪያ በዊንድዛር ቅዱስ ጊዮርጊስ ፀሎት ቤት ልዑል ኤርሚያስ ሳሕለ ሥላሴ አዲስ ዝክረ መታሰቢያ መርቀው ከፍተዋል።

Gondar-Plaque-1536x1024.jpg
The Victory of Gondar Memorial Plaque, created by the Crown Council of Ethiopia, was permanently installed at the Royal Chapel through the courtesy of HM King Charles III and unveiled by Le’ul Ermias and Lord Ashcroft, Viscount of Gondar. Credit: The Crown Council of Ethiopia

ልዑልነታቸው ለንደን አጠገብ በሚገኘው በዊንድሶር ቤተመንግስት በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተመቅደስ ውስጥ፤ ጃንሆይና የኢትዮጵያ አርበኞች ከታላቋ ብሪታኒያና የቅርብ አጋሮቿ ጋር በመሆን በ1934 ዓ.ም ተዋግተው የተቀዳጁትን ድል የሚያበስርና የሚያስታውስ፤ በብረት ላይ የተቀረጸ የጎንደር ድል የጽሁፍ ቅርስ ለከተማው በማበርከት አስመርቀዋል፡፡

Freedom-of-the-City-of-London-1.jpg
Credit: CCE

ልዑል ኤርሚያስ የጎንደርን ድል የመታሰቢያ ቅርስ ሽፋን የገለጡት የአፄ ቴዎድሮስ ልጅ፤ ልጅ ዓለማየሁ ቴዎድሮስ መቃብር ፊት ለፊት ነው።

በወቅቱም፤ የቤተመቅደሱ ካህን ጆናታን ኩር በእንግሊዝኛና በግዕዝ ቋንቋዎች ከመጽሀፈ ሄኖክ በመጥቀስ ፀሎት ማድረጋቸውንና ልዑል ኤርሚያስም ለጆናታን ኩር የኢትዮጵያንና የታላቋ ብሪታኒያን የጦር አጋርነት የሚያበስረውን የታላቁን የጎንደር ድል መዳሊያ መሸለማቸውን የዘውድ ምክር ቤቱ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።

በሌላም በኩል ለልዑል ኤርሚያስ "የለንደን ከተማ ነፃነት" ሽልማት በለንደን ከተማ ሕዳር 7 ተበርክቶላቸዋል።

Ethiopia (28).jpg
Credit: Philip Dean

ቀደም ሲልም በ1947 አያታቸው ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ ተመሳሳይ ሽልማት ከለንደን ከተማ ተቀብለዋል።


2 min read

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now