የዘውድ ምክር ቤት ፕሬዚደንቱ ኢትዮጵያውያንና የእንግሊዝ የክብር እንግዶች በተገኙበት ሕዳር 7 በተዘከረው የጎንደር ድል የእራት ግብዣ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ በአሁኑ ወቅት በዓለም ላይ ሕልፈተ ሕይወትና መፈናቀልን አስመልክቶ ትልቁ ጦርነት ኢትዮጵያ ውስጥ መሆኑን አመላክተዋል።
ይህንኑ ሲገልጡም፤
"ባለፉት ዓመታት 1.5 ሚሊየን ያህል ሰዎች ተገድለዋል፤ 26 ሚሊየን ያህል ከቤታቸው ተፈናቅለዋል። በዩክሬይንና እሥራኤል ሕልፈተ ሕይወትና ትርጉመ ሕይወት ሁኔታዎች ዓለምን በሐዘኔታ እንቀላቀላለን፤ ስለምን የመከራን ምንንነት እናውቃለንና" ብለዋል።
በዘንድሮው የጎንደር ድል በዓል በአገረ እንግሊዝ ንጉሥ ቻርልስ ሳልሳዊ ሞገስ አላባሽነት ለጎንደር ድል በክብር ለወደቁት የእንግሊዝና ኢትዮጵያ አርበኞች መዘከሪያ በዊንድዛር ቅዱስ ጊዮርጊስ ፀሎት ቤት ልዑል ኤርሚያስ ሳሕለ ሥላሴ አዲስ ዝክረ መታሰቢያ መርቀው ከፍተዋል።

The Victory of Gondar Memorial Plaque, created by the Crown Council of Ethiopia, was permanently installed at the Royal Chapel through the courtesy of HM King Charles III and unveiled by Le’ul Ermias and Lord Ashcroft, Viscount of Gondar. Credit: The Crown Council of Ethiopia

Credit: CCE
በወቅቱም፤ የቤተመቅደሱ ካህን ጆናታን ኩር በእንግሊዝኛና በግዕዝ ቋንቋዎች ከመጽሀፈ ሄኖክ በመጥቀስ ፀሎት ማድረጋቸውንና ልዑል ኤርሚያስም ለጆናታን ኩር የኢትዮጵያንና የታላቋ ብሪታኒያን የጦር አጋርነት የሚያበስረውን የታላቁን የጎንደር ድል መዳሊያ መሸለማቸውን የዘውድ ምክር ቤቱ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።
በሌላም በኩል ለልዑል ኤርሚያስ "የለንደን ከተማ ነፃነት" ሽልማት በለንደን ከተማ ሕዳር 7 ተበርክቶላቸዋል።

Credit: Philip Dean