" በአፋር ክልል የደረሰውን የንጹሓን ጭፍጨፋ ፓርቲያችን በጽኑ ያወግዛል" እናት ፓርቲ

*** እናት ፓርቲ "በዚህ አጋጣሚ መርጦ የሚያለቅሰው ዓለምአቀፉ ማኅበረሰብና መገናኛ ብዙኃን ድርጊቱን በሚገባው ልክ እንዲያወግዝ እንጠይቃለን" ሲል ውግዘትና ማሳሰቢያውን አቅርቧል።

Tigray conflict

Portrait of a girl with a scarf on the head, Afar Region, Gewane, Ethiopia. Source: Getty

እናት ፓርቲ ነሐሴ 5 ባወጣው መግለጫ በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት፣ በፈንቲ ረሱ ዞን፣ በጋሊኮማ ከተማ፣ ጋሊኮማ ጤና ጣቢያ ጦርነት ሸሽተው በተጠለሉ ንጹሓን ላይ ሐምሌ23 2013 የደረሰው አሰቃቂ ጭፍጨፋ በእጅጉ እንዳሳዘነው ጠቅሶ፤ እስከአሁን እየወጡ ባሉ መረጃዎች የጭፍጨፋው ሰለባዎች ከጦርነቱ ጋር ግንኙነት የሌላቸው ከ240 በላይ ሕጸናት፣ ሴቶችና አረጋውያን መሆናቸውን የተረዳ መሆኑን ገልጧል። 

ፓርቲው ድርጊቱን "ቅስም ሰባሪ" ብሎ የጠራው ሲሆን ሕወሓትንም በፅኑ አውግዟል። 

አያይዞም "ለተጎጂ ቤተሰቦች፣ ለክልሉ መንግስትና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ  እየገለጸ፣ ለተጎጂ ቤተሰቦችም መጽናናትን ይመኛል። ፓርቲያችን ለተጎጂ ቤተሰቦች ለሚደረግ እገዛ ሁሉ አባላቱንና ደጋፊዎቹን በማስተባበር የአቅሙን አስተዋጽዖ እንደሚያደርግ ቃል ይገባል፤ መንግስትም ይህንኑ ሚናውን እንዲወጣ አበክሮ ይጠይቃል" ብሏል።

አክሎም "በዚህ አጋጣሚ መርጦ የሚያለቅሰው ዓለምአቀፉ ማኅበረሰብና መገናኛ ብዙኃን ድርጊቱን በሚገባው ልክ እንዲያወግዝ እንጠይቃለን" ሲል ውግዘትና ማሳሰቢያውን አቅርቧል።

 

 


Share

Published

By Stringer Report

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service