ለትግራይ ሰብአዊ እርዳታ የአውሮፕላን በረራ በአዲስ አበባ በኩል መከናወን እንደሚችል መንግስት አስታወቀ

*** "የተባበሩት መንግስታት እርዳታዎችን ለማድረስ ወደ ትግራይ የሚንቀሳቀሱ አውሮፕላኖች እየተፈተሹ አዲስ አበባ ሲያርፉና ሲነሱ አስፈላጊው ትብብር ይደረግላቸዋል፤ ይሁን እንጅ በትግራይ ለሚያጋጥማቸው ማንኛውም ነገር መንግሥት ኃላፊነቱን አይወስድም" ሚኒስትር ደኤታ ሬድዋን ሁሴን

State Minister Redwan Hussien.

State Minister Redwan Hussien. Source: SBS Amharic/Demeke Kebede

ዛሬ ለዓለም አቀፍ ዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ ማብራሪያ በስካይላይ ሆቴሌ በኋላ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታው አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳነሱት የሰብአዊ ድጋፍ ለማድረግ ለሚፈልጉ ዜጎች መጥተው ማገዝ  እንዲችሉ ቪዛም እንደሚዘጋጅላቸው ተናግረዋል።

አምባሳደር ሬድዋን የተባበሩት መንግስታት እርዳታዎችን ለማድረስ ወደ ትግራይ የሚንቀሳቀሱ አውሮፕላኖች እየተፈተሹ አዲስ አበባ ሲያርፉና ሲነሱ አስፈላጊው ትብብር እንደሚደረግላቸው ገልፀዋል። ይሁን እንጅ በትግራይ ለሚያጋጥማቸው ማንኛውም ነገር መንግስታቸው ኃላፊነቱን እንደማይወስድ ተናግረዋል።

በቴሌኮምና ባንኮች መከፈት ጉዳይም ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ ማብራሪያ እንደተሰጠ የገለፁት ሬድዋን ለጋሾች የራሳቸውን ኔትወርክ መጠቀም እንደሚችሉ ፣ በክልሉ የባንክ አገልግሎት መልሶ ማስጀመርን ግን መንግስት ለጊዜው እንዳላሰበ ለትርፍ የተቋቋሙ በመሆናቸው ባንኮችንም አስገድዶ ስራ ጀምሩ ማለት እንደማይችል ይሁንና ለመክፈት ፈቃደኛ የሚሆኑ ካሉ ለመተባበር ዝግጁ መሆናቸውን አስታወቀዋል።

"ህወሓት የመብራትና የስልክ አገልግሎት መስመሮችን ቆርጦ ነበር። ለጥገና የተሰማሩ በአስሮች የሚቆጠሩ መሃንዲሶችንም ገድሏል። እነዚህን መሰረተ ልማቶች መንግስት ጠግኖ ወደ አገልግሎት መልሶ ነበር። በመሆኑም ህወሓት ይህንን የግድያ ወንጀል እየቀጠለ ባለበት በዚህ ሁኔታ የመብራትና የስልክ አገልግሎት ወደ ስራ ለማስገባት የፌዴራል መንግስት እንደሚቸገር ለዲፕሎሚቲክ ማኅበረሰቡ አስረድተናል" ብለዋል።

የፌዴራል መንግስት በትግራይ የተናጠል የተኩስ አቁም ውሳኔ ያሳለፈው በቁጥር ጥቂት የሆኑትን ወንጀለኞች ለመያዝ ተብሎ ብዙ ዋጋ መክፈል እንዲቆም መሆኑን የገለፁት አምባሳደር ሬድዋን ይሁንና መንግስታቸው የተናጠል የተኩስ አቁም ቢያደርግም በኮረም በኩል የትግራይ ልዩ ኃይል ተኩስ ከፍቶ እንደነበር ገልፀዋል።


[ ደመቀ ከበደ ፡ አዲስ አበባ ]


Share

Published

By Demeke Kebede

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service