የትግራይ ክልል መስተዳድር የክልል ምርጫ ኮሚሽን አባላትን ሰየመ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይሁንታን የተነፈገው የትግራይ ክልል ምክር ቤት በጠራው አስቸኳይ ስብሰባ ምርጫውን ለማካሔድ የኮሚሽን አመራር አባላትን መርጦ የኃላፊነት ደረጃዎችን አከፋፍሏል።

Tigray Electoral Commission

Source: Courtesy of PD

የትግራይ ክልል ምክር ቤት ሕወሓትንና ሶስት ተጨማሪ የፖለቲካ ድርጅቶችን አካትቶ ስድስተኛውን የክልል ምክር ቤት ምርጫ ለማካሔድ በወሰነው መሠረት አምስት የኮሚሽን አባላትን ሰይሟል።

በክልል ምርጫ ኮሚሽነርነትና አባልነት የተመደቡትም፤

  1. መምህር ሙሉወርቅ ኪዳነ ማርያም - የትግራይ ክልል የምርጫ ኮሚሽን ኮሚሽነር
  2. ወ/ሮ ጽጌረዳ ዲበኩሉ - የትግራይ ክልል የምርጫ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር
  3. ረዳት ፕሮፌሰር መረሳ ፀሓየ - የትግራይ ክልል የምርጫ ኮሚሽን አባል
  4.  ዶ/ር ጸጋ ብርሃን - የትግራይ ክልል የምርጫ ኮሚሽን አባል
  5. አቶ መሐመድ ሰዒድ ሐጎስ - የትግራይ ክልል ምርጫ ኮሚሽን አባል ናቸው።
ክልሉ በሚያካሂደው ምርጫ ከሕወሓት በተጨማሪ የሚሳተፉት ድርጅቶች ባይቶና፣ ሳልሳይ ወያነ ትግራይና ውናት ነፃነት ትግራይ ናቸው።

በክልሉ በአንጋፋ ተቃዋሚነት የሚታወቁት ዓረና ትግራይ ለዲሞክራሲያዊነትና ሉዓላዊነት ፓርቲና የትግራይ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ በምርጫው እንደማይሳተፉ አስታውቀዋል።

ቀደም ሲል የትግራይ ክልል ምክር ቤት  “ኮቪድ 19ኝን እየተከላከለ 6ኛውን ዙር ምርጫ ለማካሄድ የወሰነ በመሆኑ የኢፌዴሪ ህገ መንግስት በሚያዘው መሰረት ቦርዱ ውሳኔውን ተቀብሎ ምርጫውን እንዲያስፈፅም፣ምርጫውን ለማካሄድ የሚያስፈልግ የሰው ሃይልና ሎጂስቲክስ ዝግጅት እንዲያደርግ እና ውሳኔውን ለምክር ቤቱ እንዲያሳውቀን” ሲል ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥያቄ አቅርቦ ቦርዱ ሕገ መንግሥታዊ አንቀጽ 102 (1) ንና   የቦርዱን ስልጣንና ኃላፊነትን የወሰነውን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1133/2011 አንቀጽ 7.1 ን ጠቅሶ ምላሽ ሰጥቷል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አያይዞም ጁን 25 የትግራይ ክልል ምክር ቤት ምርጫ በተናጠል ላካሂድ ጥያቄን ያልተቀበለው መሆኑን አስመልክቶ በሰጠው ምላሽ፤

1. 6ኛው አገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የሚካሄድበት ጊዜ እንዲራዘም ምክንያት የሆነው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ሁኔታ እንደገና ተገምግሞ ምርጫ ማካሄድ የሚያስችል ሁኔታ መፈጠሩ እስኪረጋገጥ ድረስ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በየትኛውም የአገሪቱ ክልል ምርጫ አያካሄድም፡፡

2. በተጨማሪም ከላይ እንደተገለጸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፓለቲካ ፓርቲዎችን መመዝገብ፣ መቆጣጠር እና ማስተዳደር፣ የምርጫ ጊዜ ሰሌዳን ማውጣት፣ የምርጫውን ከተጽእኖ ነጻ እና ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ማስፈጸም ስልጣን ያለው ብቸኛ ተቋም ነው፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ ምርጫ የጊዜ ሰሌዳን፣ አፈጻጸምንም ሆነ ተያያዥ ሁኔታን የሚወስነውም ቦርዱ ብቻ ነው፡፡በመሆኑም የትግራይ ክልል ምክር ቤት በክልሉ ውስጥ 6ተኛውን ዙር የክልል ምክር ቤት ምርጫ እንዲካሄድ ውሳኔ ለመስጠት እንዲሁም ቦርዱ ይህንን ውሳኔውን ተቀብሎ ሊያስፈጽም ይገባል የሚልበት ህጋዊ መሠረት የለውም

ማለቱ ይታወሳል።

 

 

 


Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
የትግራይ ክልል መስተዳድር የክልል ምርጫ ኮሚሽን አባላትን ሰየመ | SBS Amharic