በቪክቶርያ የተጣለው ገደብ ለአንድ ሳምንት ተራዘመ

በቪክቶርያ 13 አዲስ የቫይረሱ ተጠቂዎችን ቁጥር በመመዝገቡ ገደቡ መራዘሙን ፕርምየር ዳንኤል አንድሪውስ አስታወቀዋል ።

Victorian Premier Daniel Andrews announces a Victoria lockdown (AAP)

Victorian Premier Daniel Andrews announces a Victoria lockdown (AAP) Source: AAP

ፕርምየር ዳንኤል አንድሪውስ የኮቪድ - 19 ወረርሽኙን ለማጥፋት ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገናል ስለሆነም ገደቡን ለሰባት ቀናት አራዝመናል ሲሉ ተነገሩ ።

በቪክቶርያ በማህበረሰብ ውስጥ እየተሰራጨ ያለው የኮቪድ - 19 ተያዦች ቁጥር በመጨመሩ ሳቢያ ተጥሎ የነበረው ገደብ ለተጨማሪ አንድ ሳምንት ተራዝሟል።

ፕርምየር ዳናኤል አንድሪውስ ያረጋገጡትም አምስት ቀን የነበረው ገደብ እስከ መጪው ማክሰኞ ጁላይ 27 ድረስ መራዘሙን ነው።

“ ጊዜ እንፈልጋለን በከፈተኛ የጤና ኦፊሰሮች ምክር ላይ በመመስረት ገደቡን ለተጨማሪ ሰባት ቀናት አረዝመነዋል ” ሲሉ ለሪፖርተሮች ተናግረዎል ።

“ ራሳችንን ለአደጋ ማጋለጥ አንፈልግም የማናውቀው የቫይረስ ስርጭት አለ”

ቪክቶርያ 13 አዲስ የቫይረሱ ተጠቂዎችን ቁጥር ያስመዘገበች ሲሆን እስከ ማክሰኞ ድረስ ባለው መረጃ መሰረትም 50,000 የሚሆኑ ሰዎች የኮቪድ - 19 ምርመራን አድርገዋል ።

በትናንትናው እላት የተመዘገበው 12 የተጠቂዎች ቁጥርም በአሁን ሰአት ካለው የዴልታ ቫርያንት ወረርሽኝ ጋር ተያያዝ ሲሆን ምንጩም ከኒው ሳውዝዊልስ ነው ። የአንደኛውን የቨይረስ ምንጭ ለማወቅ አሁንም በምርመራ ላይ ያለ ሲሆን የተቀሩት ዘጠኙ በለይቶ ማቆያ ይገኛሉ ።


1 min read

Published

Updated

By Tom Stayner

Presented by Martha Tsegaw


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now