“ለኢትዮጵያ ሕዝብ ሕይወቴን ከመስጠት ባሻገር… እንደ ሌባ አገሬን ትቼ አልወጣም።” - ኮማንደር ለማ ጉተማ – ክፍል 1

ሱዚ ለማ፤ ከቦቆጂ ለኢትዮጵያ ሕዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢሕዲሪ) ሸንጎ ምክትል ፕሬዚደንትነት ስለደረሱት ወላጅ አባታቸው ኮማንደር ለማ ጉተማ የሕይወት ታሪክ አንስተው ይዘክራሉ።

The Life and Times of Commander Lemma Gutema Pt 1

Lemma Gutema (L), and Suzi Lemma (R) Source: Courtesy of SLG

የኮማንደር ለማ ጉተማ የውልደት ቀዬ በአርሲ ክፍለ አገር፣ ጭላሎ አውራጃ የምትገኘው በቆጂ ናት።

 እግራቸው ሲጠና ለትምህርት ወደ አዲስ አበባ አቀኑ። የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውንም በኮከበ ፅባህ ትምህርት ቤት ፈጸሙ።

 በ1951 የኢትዮጵያ ባሕር ኃይልን ኮሌጅ ዕጩ መኮንን ሆኑ። ስልጠናቸውንም ጨርሰው በላቀ ውጤት ተመረቁ። ሲልም፤ ወደ ባሕር ማዶ አቅንተው በአገረ እንግሊዝና ዩናይትድ ስቴስ የባሕር ኃይል መኮንን ወታደራዊ ዕውቀታቸውን ከፍ አድርገው ገነቡ።
The Life and Times of Lemma Gutema Pt 1
Lemma Gutema Source: Courtesy of SLG
ወደ አገር ቤት ከተመለሱም በኋላ በ1960 የቀደማዊ ኃይለ ሥላሴ የሕግ ፋክሊቲ ከመጀመሪያዎቹ የሕግ ተማሪዎች አንዱ ሆነው በመጀመሪያ ዲግሪ ለመመረቅ በቁ።

 

ኮማንደር ለማ በውትድርና ሕይወታቸው በኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ኮሌጅ አስተምረዋል፤ በሕግ አማካሪነትና በቃኚ ጦር መርከብ አዛዥነት አገልግለዋል።

 

በሲቪል አስተዳደር በካሣ ኮሚሽን ኮሚሽነርነት፣ በሐረርጌ ክፍለ አገር አስተዳዳሪነትና በአገር አስተዳደር ሚኒስትርነት ሰርተዋል።

 

በዲፕሎማሲው ዘርፍ በጀርመን ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ የኢሕዲሪ ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው ሰርተዋል።
The Life and Times of Commander Lemma Gutema Pt 1
Lemma Gutema Source: Courtesy of SLG
በፖለቲካው ዘርፍም፤ በአዲስ አበባ የኢሠፓአኮና ኢሠፓ አንደኛ ጸሐፊ፤ ከፍ ብለውም ኢሕአዴግ የኢሕዲሪን መንግሥት እስከ ከላ ድረስ የኢሕዲሪ ሸንጎ ምክትል ፕሬዚደንት ነበሩ።
The Life and Times of Commander Lemma Gutema Pt 1
Mengistu Hailemariam (L) and Lemma Gutema (R) Source: Courtesy of SLG


ከሰባት ዓመታት እስራት በኋላም በልብ ህመም ሳቢያ የካቲት 29 – 1990 ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።


Share
1 min read

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service