Life and Legacy: Emeritus Prof Bereket Habte Selassie - Pt 5

Emeritus Prof Bereket Habte Selassie - Pt 5 Source: Courtesy of BHS
የመጀመሪያው አገር በቀል የኢትዮጵያ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግና ኋላም የኤርትራ ሕገ መንግሥት አርቃቂ ኮሚሽን ሊቀመንበር የነበሩት ፕሮፌሰር በረከት ሃብተስላሴ፤ በክፍል አምስት ቃለ ምልልሳችን የሕይወት ጉዞ ታሪካቸውን ያጠቃልላሉ። መንደርደሪያቸው በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል በባድመ ጦርነት መቀስቀስ ሳቢያ ‘ጦርነቱ ያለ ፓርላማና የሚኒስትሮች ምክር ቤት ይሁንታ እንደምን ታወጀ?’ ብለው የተቃውሞ ድምጻቸውን ካሰሙት ‘የቡድን ፲፭’ አባላት እንቅስቃሴ ነው። አሰናስለውም ለኤርትራና ለኢትዮጵያ የወደፊት ዕድል መልካም ምኞት፣ ስለ ጡረታ ዘመን አኗኗር ዘይቤያቸውና ፀፀት አለብኝ ብለው ባያስቡም፤ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የበደሏቸው ሰዎች ካሉ ይቅርታ እንዲያደርጉላቸው በመጠየቅ ይደመድማሉ።
Share




