ለረድዔት ተግባር ወደ ኢትዮጵያ ዘልቀው ሕይወታቸው ኢትዮጵያ ውስጥ ያለፈው የአሜሪካ የምክር ቤት አባል ሚኪ ሊላንድ ግብር የላቀ ከበሬታ እንዲያገኝ ጥረዋል። ስኬትም ገጥሟቸዋል።

በወቅቱ የኢትዮጵያ ፕሬዚደንት የነበሩት መንግሥቱ ኃይለማርያም ሳይቀሩ ተቀብለው አነጋግረዋቸዋል።

የፓን-አፍሪካኒዝም ዓላማ አራማጅ እንደመሆናቸውም ከአፍሪካውያን መሪዎች ጋር ተገናኝተው ተነጋግረዋል።


የመንግሥቱ ኃይለማርያም የአገዛዝ ሥርዓት በኢሕአዴግ አገዛዝ ሲተካና ኤርትራም ሉዓላዊት አገር ስትሆን፤ ኢትዮጵያውያን የጦር ምርኮኞችን ለማስፈታት ኤርትራ ድረስ ዘልቀው ከፕሬዚደንት ኢሳይያስ አፈወርቂና የጦር ምርኮኞች ጋር ተነጋግረዋል።

አሁን በቅርቡም የኢትዮጵያ ጉዳይ በብርቱ አሳስቦኛል ብለው ተነስተው ከቀድሞው የዩናይትድ ስቴትስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ከነበሩት ኽርማን ኮኸን ጋርም ‘ምን መደረግ አለበት?’ ሲሉ መክረዋል።
ሁሉን አቀፍ የሽግግር ሂደት እንዲፈጠር አሜሪካ ልዩ ሚና እንድትጫወት ምክረ ሃሳባቸውን ለኮኸን አቅርበዋል።





