Mustafa the Builder: My Somali & Ethiopian Identities Are Intertwined

Mustafa the Builder: My Somali & Ethiopian Identities Are Intertwined

Mustafa Mohammed Omar Source: Courtesy of MMO

ሙስጠፋ መሐመድ ዑመር፤ የሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ፕሬዚደንት ናቸው። ከባህር ማዶ ወደ አገረ ኢትዮጵያ ጠቅልለው የገቡት በቅርቡ ነው። የፖለቲካዊ አመራር ጉዟቸው በጠብመንጃና በፍራቻ ሳይሆን፤ በመፈቃቀር፣ መብቴን አግኝቻለሁ፣ እጠቀማለሁ በሚል ዕሳቤ የሶማሌ ሕዝብ የአገር አንድነትን እንዲያጠነክር ማድረግ እንደሆነ ይናገራሉ።


አቶ ሙስጠፋ የግብርና ምጣኔ ሐብት ባለሙያ ሲሆኑ፤ ዘለግ ላሉ ጊዜያት የተባበሩት መንግሥታት ሠራተኛ ሆነው በአፍሪካና መካከለኛው ምሥራቅ ተዘዋውረው ዓለም አቀፍ ግልጋሎቶችን አበርክተዋል። በሂደቱም ልምድ ቀስመዋል፤ ክህሎታቸውን አዳብረዋል።
Mustafa the Builder: My Somali & Ethiopian Identities Are Intertwined
Mustafa Mohammed Omar Source: Courtesy of PD
በሶማሌ ክልል ሰላምን ማስፈን፣ የሰብዓዊ መብቶችን ጥሰትን መግታት፣ ለሕዝብ ታማኝ አገልጋይ መሆን  ከዘርፈ ብዙ ተልዕኮቻቸው መካከል ጥቂቶቹ መሆናቸውን ያመላክታሉ።

ባለፉት በርካታ ዓመታት በሶማሌ ክልል ተከስተው ስለነበሩ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን ነቅሰው ሲናገሩም፤ ግድያ፣ ሰቆቃ፣ መንደሮችን ማቃጠል፣ በርካታ ሰዎችን ለስደት መዳረግ፣ ለወራት መጸዳጃ ቤት ውስጥ ሰዎችን ማሰር፣ በጅብና በነብር እስረኞችን ማሸበርን በዋነኘነት ያነሳሉ። ይህ ግፍ የተፈጸመበት የጂግጂጋ እሥር ቤት ወደ ሙዚየም ይቀየራል በማለትም ይገልጣሉ።

ሐምሌ 28 በጂግጂጋ የተካሄደው የአመጽ ጥቃት የተወጠነው በክልሉ ብቻ የተወሰነ ብጥብጥን ለማስነሳት ሳይሆን፤ በደገኛና ቆለኛው፣ በሙስሊሙና ክርስቲያኑ መካከል ግጭቶችን ፈጥሮ አገሪቷን ብጥብጥ ውስጥ ለማስገባት እንደነበረ ይጠቁማሉ።

ይህን ያስፈጸመውም መዋቅርና በጀት የነበረው  “ሔጎ” የሚባል በህቡዕ ይንቀሳቀስ የነበረ የወጣቶች ድርጅት እንደነበር ጠቅሰው፤ በአሁኑ ወቅት ግና አብዛኛዎቹ መዋቅሮቹ እንደፈራርሱና ቀሪዎቹንም በማፈራረስ ላይ እንዳሉ ያስታውቃሉ።

የማንነት ፖለቲካና የዜግነት ፖለቲካን አስመልክቶ ያላቸው አተያይ አደጋዎችን ጠቋሚና መፍትሔን አመላካች ነው።

“ማንነት ላይ ያተኮረ ፖለቲካ ዞሮ-ዞሮ ወደ ግጭት ነው የሚያመራው። ከማንነት ፖለቲካ ወደ ፖለቲካዊ እሳቤ ቶሎ ብንሸጋገር፤ በዜግነት ላይ ያተኮረ የመብት ጥያቄዎች የሚመለሱባት አገር ብንመሰርት ደስ ይለኛል” ባይ ናቸው።  

ይህንኑ አንድነት ከክልላቸው ለመጀመር  የሶማሌን ባሕልና ታሪክ የሚዘክሩ ነገሮችን መሥራት እንዳለባቸው፤ የሶማሌን አንድነት ማጉላቱ የጎሳ ትንቅንቅን ለመክላትና ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ወገኖች ጋር የባሕል፣ የታሪክና ልምድ ልውውጦችን በማድረግ መቃቃሮችን በመቻቻል ባሕል ለመተካት ያስባሉ።

በተለይም “ለበርካታ ዓመታት በአማራው ላይ ስር የሰደደ አሉታዊ ስብከቶች ስለነበሩ፤ የመጀመሪያ ልዑካን ቡድናችንን በቅርቡ ወደ አማራ ክልል እንዲሄድ እናደርጋለን” በማለት የአንድነትና ብሔራዊ ማንነት ግንባታ ውጥናቸውን አጋርተውናል።
Mustafa the Builder: My Somali & Ethiopian Identities Are Intertwined
Mustafa Mohammed Omar Source: SBS Amharic
በዘር ላይ ያተኮረ ፖለቲካ ዘላቂነት የሌለው ስለመሆኑ ፅኑዕ እምነት እንዳላቸው ገልጠውም፤ ጥሩ-ጥሩ ምሁራን ተሰባስበው በመወያየት አዲስ ዕሳቤ፤ አዲስ ራዕይ መፍጠር አለባቸው ሲሉ ያሳስባሉ።

በእሳቸው በኩል ለኢትዮጵያ ያላቸውን ራዕይ ሲገልጡ፤ “የእኔ ራዕይ ሁሉን አካታች፤ ሁሉም ተጠቃሚ በሚሆንባት ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ፤ ሁሉም ዜጋ በፈለገው ቦታ የሚሰራባትና የሚኖርባት፣ ሰላም የሰፈነባት፣ ሲልም ለምሥራቅ አፍሪካ ማዕከል የምትሆንበት ነው። በሶማሌ አካባቢ የምናደርጋቸውም እንቅስቃሴዎች ለዚያ ትልቅ ራዕይ አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ነው” ይላሉ።
Mustafa the Builder: My Somali & Ethiopian Identities Are Intertwined
Kassahun Seboqa Negewo (L), and Mustafa Mohammed Omar (R) Source: SBS Amharic
ሩቅ አሳቢ፤ ቅርብ አዳሪ እንደማይሆኑ ተስፋችን ነው።


Share
Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service