Remembering the former Ethiopian President Girma Wolde-Giorgis

Remembering the former Ethiopian President Girma Wolde-Giorgis

Former Ethiopian President Girma Wolde-Giorgis Source: Courtesy of PD

የቀድሞው የኢፌዴሪ ፕሬዚደንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ፤ 94ኛውን ዕለተ ልደታቸውን አሥመራ ላይ ለማክበር ቀን ቆርጠው ነበር። ዕሳቤያቸው ሳይሆን ቀርቶ ዲሴምበር 15 – 2018 ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።


የቀድሞው የኢፌዴሪ ፕሬዚደንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ፤ በቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ዘመነ መንግሥት በውትድርናው ዓለም የመቶ አለቃነት ማዕረግ ደርሰዋል።  የዘውድ ሥርዓቱ ፓርላማ አባል ሆነው ሳለ የኢትዮጵያ ፓርላማ የዓለም ፓርላማ አባል እንዲሆን፤ የጅራፍ ግርፋት ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲከላ የጎላ ሚና አበርክተዋል።

አስተዋፅዖዎቻቸውም የሕይወት አሻራዎቻቸው ነፀብራቅ ሆነዋል።

በዘመነ ኢሕአዴግም በቾን ወክለው በግል ተወዳዳሪነት የፓርላማ አባል ሆነዋል። ሲልም፤ ለ12 ዓመታት የኢፌዴሪ ፕሬዚደንት ለመሆን በቅተዋል።

በዘመነ ፕሬዚደንትነታቸው ኢትዮጵያ ውስጥ የሞት ቅጣት እንዲቀር ትታረዋል። ለፍርድ ቤት ይሙት በቃ ብያኔ ይሁንታን ላለመቸር ‘የሰው ልጅ ሕይወት በሰው እጅ እንዲነጠቅ ፕሬዚደንታዊ ፊርማዬን አላሰፍርም’ ብለው ጸንተዋል።

በሕይወት ሳሉ ብርቱ ምኞታቸው ኢትዮጵያና ኤርትራን ማስታረቅ ነበር።  የእሳቸው ጉልህ ሚና አሻራ ባይኖርበትም ሁለቱ አገራት የሰላም ውል ሲዋዋሉ ለመመልከትና ከፕሬዚደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋርም ለመገናኘት በቅተዋል።
Remembering the former Ethiopian President Girma Wolde-Giorgis
የሰላም ስምምነት - ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ (ግራ) እና ፕሬዚደንት ኢሳያስ አፈወርቂ (ቀኝ) Source: Courtesy of PD
ባለፈው ወርሃ ኦክቶበር ወደ ኢትዮጵያ ለሥራ ተጉዘን በነበረት ወቅት ትህትና በተመላው ግብዣቸው ሳቢያ ከመኖሪያ ቤታቸው ተገኝተን በግል አውግተናል። ወጎቹ ግላዊ በመሆናቸው ለአየር የሚበቁ አይደሉም።
Remembering the former Ethiopian President Girma Wolde-Giorgis
የቀድሞው የኢፌዴሪ ፕረዚደንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ (ግራ) እና ጋዜጠኛ ካሳሁን ሰቦቃ (ኦክቶበር 12 - 2018 በቀድሞው ፕሬዚደንት መኖሪያ ቤት) Source: SBS Amharic
ለዛሬው ግና ጃኑዋሪ 2 – 2014 ክቀድሞው ፕሬዚደንት ጋር ያደረግነውን ቃለ ምልልስ መዘከሪያ ይሆን ዘንድ ይዘን ቀርበናል።

 


Share
Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service