We Should Offer Our Apologies: DPM Demeke Mekonnen (አባ መላ) – Pt 2

We Should Offer Our Apologies: DPM Demeke Mekonnen (አባ መላ) – Pt 2

Deputy Prime Minister Demeke Mekonnen Source: SBS Amharic

በክፍል ሁለት ቀጣይና መደምደሚያ ቃለ ምልልሳችን፤ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከመምህርነት ወደ ፖለቲካው ዓለም እንደምን ተስበው እንደዘለቁ፤ ወደ ቁጥር ሁለት የሥልጣን እርከን ላይ እንዴት እንደደረሱ፤ በምን ሳቢያ “አባ መላ” እንደተሰኙ፤ ባለፉት ሶስት የለውጥ ንቅናቄ ዓመታት የነበሩትን ፈታኝ ሁኔታዎች፣ የእሳቸውን መንታ መንገድ ላይ መድረስና ሚና አንስተው ይናገራሉ።


በማኅበራዊ ሕይወት ውስጥ “ትህትናና ቅንነት” የመልካም ስብዕና መገለጫ ናቸው። በፖለቲካው ዘርፍ ግና ዝንቅ ዕንድምታዎች አሏቸው። ሽኩቻ፣ መጠላለፍና አንጃ ገንነው ባሉበት የፖለቲካ መስክ “ትሁትና ቅን” ሆኖ መዝለቅ አዋኪ ነው። ይሁን እንጂ ስለ አቶ ደመቀ መኮንን ሲነሳ፤ “ትሁት” ፣ “ቅን” የሚሉ የባህሪይ ማጣቃሻዎች ይደመጣሉ።

አቶ ደመቀ ወደ ፖለቲካው መድረክ ብቅ ያሉት ገና በ20ዎቹ ለጋ የወጣትነት ዕድሜ ዘመናቸው በመሆኑ፤ አሁን ሰልፋቸው ከጎምቱ ፖለቲከኞች ተርታ ነው። ከዕድሜያቸው ግማሽ በላይ ለ26 ዓመታት በኢትዮጵያ የተለያዩ የፖለቲካ አመራር ዕርከኖች ላይ ቆይተዋል።

ከመምህርነት በቀጥታ የዘለቁት ወደ አማራ ክልል ከፍተኛ አመራር ነው። አነሳሳቸው ከክልል መንግሥቱ ቁጥር ሶስት የሥልጣን እርካብ ሲሆን፤ ምክትል ፕሬዚደንት፣ የብአዴን/አዴፓ ሊቀመንበር፣ የፌዴራል ሚኒስትርና ሲልም አሁን ካሉበት የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር መንበር ላይ ለመሰየም በቅተዋል።
We Should Offer Our Apologies: DPM Demeke Mekonnen (አባ መላ) – Pt 2
Deputy Prime Minister Demeke Mekonnen Source: Courtesy of PD
በዘመናዊ ፖለቲካ ራስን ለሕዝብ አዳምቆ መሸጥ ግድ በሚልበት ዘመን፤ ስለራሳቸው ለመናገር ቁጥብ ናቸው። በቅንጭቡም ቢሆን በእርሳቸው አንደበት ስለ ደመቀ መኮንን ማንነት እንዲነግሩን በማንሳታችን ግና ‘ከቤተሰብ ሕይወታቸው ጀምሮ ዕርቀ ሰላምን ማውረድ መውደዳቸውን፣ ሁሉንም ሰው እኩል የማየት፣ የማድመጥ፣ ነገሮችን አጣጥሞ ወደ መፍትሔ የመውሰድ ተሰጥዖዎቻቸው “አባ መላ” እንዳሰኟቸው’ ከአንደበታቸው ለማድመጥ በቅተናል።

የአጼ ምኒልክን ቀኝ እጅ ፊታውራሪ ሀብተጊዮርጊስ ዲነግዴ “ሀብቴ አባ መላ”ን ያስታውሷል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ፤ አስተዳደጋቸው ከኦሮሞ፣ አገው፣ ሺናሻና የጉምዝ ተወላጆች ጋር በመሆኑ ለብዝሃነት ባይተዋር እንዳልሆኑ፤ ያም የኢትዮጵያን ዝንቅ ብሔረሰባዊ ገጽታና ምልከታዎች እንዲረዱ፤ በቀላሉ ከሰዎች ጋር ተግባብተውና ተከባብረው ለመኖር አዎንታዊ አስተዋጽዖ እንዳበረከተላቸው ይገልጣሉ።

በሶስቱ የለውጡ ጉዞ ዓመታት ውስጥ፤ አይነኬ የሚባሉ አስተሳሰቦችንና ተቋማትን መታገል፤ እንደ ብአዴን ሊቀመንበርነታቸውና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነታቸው የብአዴንን ፍላጎት ከፌዴራል ጋር አጣጥሞ መሄድ ፈታኝ እንደነበሩ፤ አቶ ለማና ዶ/ር ዐቢይ ሲመጡም በመመጋገብ አሁን ለተደረሰበት ደረጃ መብቃት መቻሉን በምልሰት ነቅሰው ያወጋሉ።
We Should Offer Our Apologies: DPM Demeke Mekonnen (አባ መላ) – Pt 2
DPM Demeke Mekonnen (L), and PM Abiy Ahmed (R) Source: Courtesy of PD
ስለ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ሲያነሱም፤ “ትሁት፣ ብርቱ ሠራተኛ፣ ይበልጡኑ ወደ ቀለም ትምህርት የሚያተኩሩ...” ብለው በማንሳት፤ “ሥልጣን ይበቀኛል። እኔ የመፍትሔው አካል ልሁንና አገርን ልታደግ ማለት፤ በደም ሥልጣን ሲዘዋወር በነበረባት አገር ውስጥ ትልቅ ውርሰ አሻራ ሆኖ ሊወሰድ የሚችል ነው” ሲሉ ታሪክ የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም በማለፊያ ሚዛኑ እንዲመዝናቸው ይሻሉ።
We Should Offer Our Apologies: DPM Demeke Mekonnen (አባ መላ) – Pt 2
Former PM Hailemariam Desalegn (L), and DPM Demeke Mekonnen (R) Source: Courtesy of PD
ስለራሳቸው ውርሰ አሻራ ግና የኢትዮጵያ ሕዝብ ተገቢ የሚለውን የታሪክ ሥፍራ ቢቸራቸው ይወዳሉ።
አቶ ደመቀ በሁነኛ ማሳሰቢያቸው፤ “ባለፉት 27 ዓመታት ያጎደልናቸው፤ ያጠፋናቸው ነገሮች አሉ። ይቅርታ መጠየቅ አለበት። ይቅርታ የምንጠይቅባቸው ጉዳዮች አሉ” ይላሉ።
የአገር ቁስል እንዲሽር፤ ጠባሳው እንዲደበዝዝ።     
We Should Offer Our Apologies: DPM Demeke Mekonnen (አባ መላ) – Pt 2
DPM Demeke Mekonnen (L), and Kassahun Seboqa (R) Source: SBS Amharic


     

 


Share
Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service