ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከተማ አስተዳደሩ ያስጠናውን የመሬት ወረራና ህገ ወጥ የኮንደሚኒየም ቤቶች ቅርምት በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል።
በዛሬው መግለጫቸው እንደተናገሩት በአዲስ አበባ ፡
~ 1,338 ሄክታር (389,955 ካሬ) መሬት ተወርሯል፡፡
~ 322 ህንፃዎች ባለቤት የላቸውም፡፡
~ 21,695 የጋራ መኖርያ ቤቶች በህገወጥ ሁኔታ ተይዘዋል፡፡
~ 14,641 መኖሪያና ለንግድ የተከራዩ የቀበሌ ቤቶችን ያለ አግባብና በህገ-ወጥ ይዞታነት ይገኛሉ፡፡
~ በህገ-ወጥ ወረራ የተያዘው መሬት በገንዘብ ሲተመን ከ14 ቢሊየን ብር በላይ ይገመታል፡፡
~ በሪል ስቴት አልሚዎች፣ በግለሰቦች፣ በሀይማኖት ተቋማትና በቡድን በመደራጀትና መንደር በመመስረት ጭምር በሚገለፅ መልኩ የመሬት ወረራ ተፈፅሟል፡፡
~ 21,695 የጋራ መኖርያ ቤቶች በህገወጥ መንገድ የተያዙ ናቸው፡፡
~ 75% የኮንዶሚኒየሞች የተያዙት ባልተመዘገቡና ባልቆጠቡ ሰዎች ነው፡፡
~ 18,423 የኮንደሚንየም ቤቶች በህገወጥ መንገድ የተያዙ ናቸው፡፡
~ 10,565 የቀበሌ መኖሪያ ቤቶች በህገወጥ መንገድ የተያዙ ናቸው፡፡
~ 234 የቀበሌ ቤቶች የጠፉ ቤቶች ናቸው፡፡
~ 537 የቀበሌ ቤቶች በህገወጥ መንገድ ወደ ግል ቤትነት የዞሩ ናቸው።

