"በአዲስ አበባ በሕገ ወጥ ወረራ የተያዘው መሬት በገንዘብ ሲተመን ከ14 ቢሊየን ብር በላይ ይገመታል" ም/ከንቲባ አዳነች አቤቤ

*** 1,338 ሄክታር (389,955 ካሬ) መሬት ተወርሯል፤ 21,695 የጋራ መኖርያ ቤቶች በሕገ ወጥ ሁኔታ ተይዘዋል፡፡

Adanech Abiebie

Adanech Abiebie, Deputy Mayor of the City of Addis Ababa Source: Adanech Abiebie/Twitter

 ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከተማ አስተዳደሩ ያስጠናውን የመሬት ወረራና ህገ ወጥ የኮንደሚኒየም ቤቶች ቅርምት በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል።

 በዛሬው መግለጫቸው እንደተናገሩት በአዲስ አበባ ፡

 ~ 1,338 ሄክታር (389,955 ካሬ) መሬት ተወርሯል፡፡

~ 322 ህንፃዎች ባለቤት የላቸውም፡፡

~ 21,695 የጋራ መኖርያ ቤቶች  በህገወጥ ሁኔታ ተይዘዋል፡፡

 ~ 14,641 መኖሪያና ለንግድ የተከራዩ የቀበሌ ቤቶችን ያለ አግባብና በህገ-ወጥ ይዞታነት ይገኛሉ፡፡

~ በህገ-ወጥ ወረራ የተያዘው መሬት በገንዘብ ሲተመን ከ14 ቢሊየን ብር በላይ ይገመታል፡፡

~ በሪል ስቴት አልሚዎች፣ በግለሰቦች፣ በሀይማኖት ተቋማትና በቡድን በመደራጀትና መንደር በመመስረት ጭምር በሚገለፅ መልኩ የመሬት ወረራ ተፈፅሟል፡፡

~ 21,695 የጋራ መኖርያ ቤቶች በህገወጥ መንገድ የተያዙ ናቸው፡፡

~ 75% የኮንዶሚኒየሞች የተያዙት ባልተመዘገቡና ባልቆጠቡ ሰዎች ነው፡፡

 ~ 18,423 የኮንደሚንየም ቤቶች በህገወጥ መንገድ የተያዙ ናቸው፡፡

~ 10,565 የቀበሌ መኖሪያ ቤቶች  በህገወጥ መንገድ የተያዙ ናቸው፡፡

~ 234 የቀበሌ ቤቶች የጠፉ ቤቶች ናቸው፡፡

~ 537 የቀበሌ ቤቶች በህገወጥ መንገድ ወደ ግል ቤትነት የዞሩ ናቸው።


1 min read

Published

Updated

By Stringer Report


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now