የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለ12 ምሁራን የፕሮፌሰርነት ማዕረግ መስጠቱን ይፋ አድርጓል።
ዩኒቨርሲቲው ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ በዩኒቨርስቲው የሚመለከታቸው የትምህርት ክፍሎች ተመርምሮ፣ በየኮሌጆች አካዳሚክ ጉባዔዎች ተፈትሾ፣ በዩኒቨርስቲው ሴኔት ታይቶ እና ይሁንታ አግኝቶ የቀረበልኝን መረጃ ተመልክቼ ለ12 ምሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቻለሁ ብሏል የዩኒቨርስቲው የሥራ አመራር ቦርድ።
የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የተሰጣቸው፤
- ፕሮፌሰር ይልማ ስለሺ ፣
- ፕሮፌሰር አለሙ መኮንን፣
- ፕሮፌሰር አለማየሁ ገዳ፣
- ፕሮፌሰር በርሲሳ ኩምሳ፣
- ፕሮፌሰር ገበየሁ ጎሹ፣
- ፕሮፌሰር ሙሉጌታ አጥናፉ፣
- ፕሮፌሰር ጌታቸው ተረፈ፣
- ፕሮፌሰር አሰፋ ፍስሃ፣
- ፕሮፌሰር ንጋቱ ከበደ፣
- ፕሮፌሰር ግርማ ዘርአዮሐንስ፣
- ፕሮፌሰር ሽመልስ አድማሱ እና
- ፕሮፌሰር አታላይ አየለ (ዶ/ር) ናቸው።
Share

