SKIP TO MAIN CONTENT

በአፋር የጎርፍ ተፈናቃዮች የአስቸኳይ እርዳታ ጥሪ እያቀረቡ ነው

ከ130 ሺህ በላይ የአፋር ክልል ደቡባዊ ዞን ነዋሪዎች በጎርፍ አደጋ ተፈናቅለዋል

Afar flood
Source: Courtesy of PD

1 min read

Published

By Stringer Report


Skip to article content

በአፋር ክልል ደቡባዊ ዞን በአምስት ወረዳዎች የአዋሽ ወንዝ ባደረሰዉ የጎርፍ አደጋ ከ130ሺ በላይ ሰዎች መፈናቀላቸዉን የአፋር ክልላዊ መንግሥት ገለጠ፡፡

ምንም እንኳ የክልሉ መንግሥት የአዋሽ ወንዝ ደቅኖት ያለውን የጎርፍ አደጋ ለመገደብ የክልሉ መንግሥት ከፌደራል መንግሥትና አዋሽ ተፋሰስ ባለስልጣን ጋር በርካታ ጥረቶችን ቢያደርግም የክረምት ዝናቡ መጠን ከፍተኛ በመሆኑ ከክልሉ አቅም በላይ መሆኑ ተነግሯል፡፡

በጎርፍ ተከበው ያሉትን ሰዎች ሕይወት ለመታደግ ሁለት ሂሊኮፕተሮች ሰዎችን ከሥፍራው የማውጣት ተግባራትን እየፈጸሙ ነው።

የጎርፍ አደጋው በአፋር ክልል ደቡባዊ ዞን ባደረሰው ጉዳት ሳቢያ የአገልግሎት ተቋማትና መሠረተ ልማቶች የወደሙ ሲሆን በሺዎች ሄክታር የሚቆጠር ማሳም ከጥቅም ውጪ ሆኗል።

በጎርፉ አደጋ ለመፈናቀል የተዳረጉት ወገኖች አስቸኳይ የሰብዓዊ ድጋፍ እርዳታዎችን መንግሥት ፈጥኖ እንዲያደርስላቸው እየጠየቁ ነው፡፡


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Stream now